በርካታ መጠን ያላቸው የውጭ ሀገራት ገንዘቦችን በማተምና ጥቁር ገበያን በማስፋፋት ወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦች ፍርድ ቤት ቀረቡ። ተጠርጣሪዎቹ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ተረኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርበው ጉዳያቸው ታይቷል።
የፀሃይ ሪል ስቴት ዋና ስራ አስኪያጅ ኪያ ዦንግን ጨምሮ ዘጠኝ የውጭ ሀገራት ዜጎች እና ሶስት ኢትዮጵውያን ተጠርጣሪዎች ናቸው ፍርድ ቤት የቀረቡት።
መርማሪ ፖሊስ ግለሰቦቹ በርካታ መጠን ያላቸው የውጭ ሀገራት ገንዘቦችን በማተምና ጥቁር ገበያን በማስፋፋት ወንጀል መጠርጠራቸውን ለችሎቱ አስረድቷል፡፡
በቁጥጥር ስር በዋሉበት ወቅትም የተለያዩ የውጭ ሀገራት ገንዘቦች የሚታተሙባቸው ማተሚያ ማሽኖችና ለግብዓት የሚያገለግሉ ኬሚካሎች እንዲሁም በርካታ ዩሮ፣ የአሜሪካ ዶላርና የሌሎች ሀገራት ገንዘቦች መያዙን ፖሊስ ጠቅሷል።
ተጠርጣሪዎቹ ላይ የተጀመሩ ሰፊ የምርመራ ስራዎችን አከናውኖ እና የተናጠል ተሳትፏቸውን ለይቶ ለመቅረብም የ14 ቀን ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል። ከአራተኛ ተጠርጣሪ ውጪ ያሉ ግለሰቦች ከወንጀል ድርጊቱ ጋር ግንኙነት እንደሌላቸው ገልጸዋል።
በተጨማሪም የተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች የግለሰቦቹ የወንጀል ተሳትፎ ባልተገለጸበት ሁኔታ ላይ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ሊሰጥ አይገባም ሲሉ ተከራክረዋል።
የፀሃይ ሪል ስቴት ዋና ስራ አስኪያጅ ኪያ ዦንግን የተባሉት ግለሰብ በበኩላቸው÷ የተገኘው የውጭ ሀገራት ገንዘብ ማተሚያ በእርሳቸው ቤትና ቢሮ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የወንጀል ድርጊቱ የሚገናኘው ከእርሳቸው ጋር ብቻ መሆኑን ገልጸው÷ ሌሎች ተጠርጣሪዎች ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት እንደሌላቸው ለችሎቹ አብራርተዋል።
መርማሪ ፖሊስ በበኩሉ÷ ተሳትፏቸው አልተገለጸም ተብሎ የተነሳውን መከራከሪያ በሚመለከት በቀጣይ ተሳትፏቸውን ለይቶ በስፋት ምርመራውን አከናውኖ እንደሚቀርብ ገልጾ መልስ ሰጥቷል።
የግራ ቀኙን ክርክር የተከታተለው ጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ተጠርጣሪዎች ላይ ተጨማሪ የማጣሪያ ምርመራ መደረግ እንዳለበት በማመን የተጠርጣሪዎቹን የዋስትና ጥያቄ ለጊዜው ውድቅ አድርጎታል።
ፖሊስ በቀጣይ ቀጠሮ የተጠርጣሪዎችን የወንጀል ተሳትፎ ለይቶ እንዲያቀርብ ከነሐሴ 26 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ የሚታሰብ የ12 ቀን የምርመራ ጊዜ ፈቅዷል።
በሌላ በኩል ፍርድ ቤቱ ተጠርጣሪዎቹ ከቤተሰብ ጋር እንዲገናኙ እና ሕክምና ማግኘት የሚፈልጉም ሕክምና እንዲያገኙ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
በታሪክ አዱኛ FBC
- በትግራይ የጊዚያዊ አስተዳደሩና የትህነግ አለመግባባት ከፍተኛ ስጋት ፈጥሯል – ጎራ የለየ ግጭት?በትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደርና በህወሐት መካከል ያለው የስላጣን ሽኩቻ ተካሮ አንዱ በአንዱ ላይ የስም ማጥፋት ዘመቻው በግላጭ እየተካሄደ ከመሆኑም አልፎ… Read more: በትግራይ የጊዚያዊ አስተዳደሩና የትህነግ አለመግባባት ከፍተኛ ስጋት ፈጥሯል – ጎራ የለየ ግጭት?
- የአባይ ድልድይ ተመረቀ፤ ፋኖ ኢላማውን የጠበቀ ጥቃት ሰነዘርኩ አለ፤ አብይ አሕመድ “መገዳደል ይብቃ” አሉበተመረጡ ቦታዎች፣ የግልና የመንግስት ተቋማት ላይ ቦንብ ማፈንዳቱን ፋኖ አስታወቀ። ይህን ያስታወቀው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ የአባይ ድልድይን ለመመረቅ… Read more: የአባይ ድልድይ ተመረቀ፤ ፋኖ ኢላማውን የጠበቀ ጥቃት ሰነዘርኩ አለ፤ አብይ አሕመድ “መገዳደል ይብቃ” አሉ
- ኢትዮጵያ በአሜሪካ የሚኖሩ “ተፈላጊዎች” ተላልፈው እንዲሰጧት ጥያቄ አቀረበችአሜሪካ ተቀምጠው የኢትዮጵያን ሰላም የሚያውኩ ተፈላጊዎችን ሀገሪቱ አሳልፋ በመስጠት ትብብር እንድታደርግ የፌደራል ፖሊስ መጠየቁ ተገለጸ። በጀርመን በተመሳሳይ ስራ መጀመሩ… Read more: ኢትዮጵያ በአሜሪካ የሚኖሩ “ተፈላጊዎች” ተላልፈው እንዲሰጧት ጥያቄ አቀረበች
- ሃሰተኛ የተባሉ የዩቲዩበር ባለቤቶች ተያዙ፤ በአንድ ተጠርጣሪ ብቻ ስምንት የዩቲዩብ ቻናል ተከፍቷልፈቃድ ሳይኖራቸው በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስምንት አማረ እና ቤተሰቦቹ በተባለ ህንፃ ላይ ቢሮ ተከራይተው ሃሰተኛና የፈጠራ ወሬ ሲያሰራጩ… Read more: ሃሰተኛ የተባሉ የዩቲዩበር ባለቤቶች ተያዙ፤ በአንድ ተጠርጣሪ ብቻ ስምንት የዩቲዩብ ቻናል ተከፍቷል
- “ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋግጠዋል”፤ የሚለው ዜና የአማራ ፖለቲካን ቀየረበሱዳን ለአንድ ዓመት የዘለቀው የእርስ በእርስ እልቂት ብዙ ተዋንያኖች አሉበት። ከአርቡ ዓለም፣ ከአውሮፓ፣ ከአፍሪቃ፣ ሩሲያና አሜሪካንን ጨምሮ የተለያዩ አካላት… Read more: “ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋግጠዋል”፤ የሚለው ዜና የአማራ ፖለቲካን ቀየረ