የአፍሪካ አገራት ወደ ብሪክስ የመጉረፍ ስሜት ይፋ ሲሆን የቡድን 20 አባል ሀገራት ሃምሳ አምስት አባል አገራትን ያቀፈውን የአፍሪካ ህብረትን ቋሚ አባል አድርጎ መቀበሉ ይፋ አደረገ። የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኒው ደልሂ እየተካሄደ ባለው የቡድን 20 ጉባኤ ላይ የአፍሪካ ህብረት ቡድኑን መቀላቀሉን ገልጸዋል። ውሳኔው ለአፍሪካ የጸጥታው ምክር ቤት አባልነት ምልክት ሆኖ ተወስዷል።
የአፍሪካ ህብረት የቡድን 20 ቋሚ አባል እንዲሆን የቀረበውን ምክረ ሀሳብ ሁሉም የአባል ሀገራቱ መሪዎች እንደተስማሙበት ተመልክቷል። በኢንደስትሪ የበለጸጉና ከአዳጊ አገራት የላቀ የምጣኔ ኃብት ዕመርታ ያስመዘገቡት አገራት መሰባሰቢያ የሆነው ህብረቱ አፍሪካ በአንድ ድምጽ መወከሏን በሕንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ንሬንድራ በኩል ይፋ አድርጓል።
በዚህም መሰረት የወቅቱ የአፍሪካ ህብረትን ሊቀመንበር የሆኑትን የኮሞሮስ ፕሬዚዳንት አዛሊ አሱማኒ በቡድን 20 ለህብረቱ የተዘጋጀውን መቀመጫ እንዲይዙ ተጋብዘው ስፋራቸውን ወስደዋል።
ደቡብ አፍሪቃ የተካሄደው የብሪክስ ስብሰባ ኢትዮጵያን ጨመሮ ስድስት አገራትን መቀበሉን ተከትሎ የቡድን ሃያ አገራት አፍሪኪአን በአባልነት ለመቀበል ዝግጁ መሆናቸውንና ግብዣ ማቅረባቸውን የሕንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ንሬንድራ አስታውቀው እንደነበር ይታወሳል።
ቢቢሲ ይህን ዜና አስታኮ የሚከተለውን ዘገባ አካቷል። በቡድን 20 አገራት ጉባኤ ላይ ከሚነሱ ነጥቦች አንዱ የዩክሬን ጉዳይ የነበረ ሲሆን፣ ቢቢሲ ይፀድቃሉ ከተባሉ ሰነዶች መካከል የተመለከተው ሰነድ እንደሚጠቁመው ስለ ዩክሬን እስካሁን የተጠቀሰ ነገር የለም። ሰነዱ የባንክ ዘርፍን ማሻሻልና ክሪፕቶከረንሲን መቆጣጠር ጨምሮ ሌሎችም ነጥቦችን ያካተተ ነው።
በሌላ በኩል የሕንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሕንድን ‘ባሐራት’ በሚል ስም መጥራታቸው ውዝግብ ፈጥሯል። አገሪቷ ስሟን በይፋ ስለመቀየሯ እስካሁን የተባለ ነገር ግን የለም።
ሌላው በጉባኤው የሚነሳው የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ ነው። ታዳጊ አገራት የበለጠ ተጎጂ ስለሚሆኑ ካደጉ አገራት አንዳች መተማመኛ ሊሰጣቸው እንደሚገባ ሲገለጽ ቆይቷል። የመጀመሪያው የቡድኑ ውይይት አንድ ምድር ወይም ‘One Earth’ የሚባል ሲሆን የአካባቢ ጉዳይን የተመለከተ ይሆናል።
ታዳጊ አጋራት በሕንድ ተወክለው በሚካሄደው ውይይት ሃብታም አገራት የካርበን ልቀትን ለመቆጣጠር የሚደረገውን ጥረት በገንዘብ፣ ቴክኖሎጂና መሠረተ ልማት እንዲደግፉ እንደሚጠይቅ ተገልጿል።
- የበርሊን ማራቶን ባለማዕረግ ትግስት እነ ዱቤ ጂሎ ቢሳተፉ ታዝረከርካቸው ነበርበማራቶን ከሁለት ደቂቃ በላይ ማሻሻል እጅግ የሚደነቅና ያልተለመደ ነው። ባለሙያዎቹ ወይም አሰልጣኞቹ የሮጠችበትን ፍጥነት በሰዓትና ርቀት ከፋፍለው ቢያቀርቡት ምን አልባትም ወንዶችን የሚገዳደር ፍጥነት ተጠቅማ ሮጣለች። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ተቴክኒክ ዳይሬክተርና የአትሌቶች ኮሚሽን ሰብሳቢ የነበሩት የዛሬው የተከበሩ ዱቤ ጅሎ አይነቱን ሯጮችን አዝረክርኮ ማሸነፍ የሚያስችላትን ሃይል አሳይታለች። የበርሊና ባለ ማዕረግ ትዕግስት!! ተግስት … Read moreContinue Reading
- የባህር ዳር ነዋሪዎች- ኢትዮጵያን ዜጎች በሁሉም ቦታ እኩል የሚስተናገዱባት ሀገር ማድረግ ይገባልየባህር ዳር ነዋሪዎች የሕዝብን ጥያቄ የመፍታት አቅም፣ ፍላጎት እና ቅንነት ያለው አመራር በመፍጠር ሕዝብን መካስ እንደሚያስፈልግ፣ ኢትዮጵያ በዘር ከመገፋፋት እና ከመጠቃቃት ነጻ የኾነች ፣ዜጎች በሁሉም ቦታ እኩል የሚስተናገዱባት ሀገር እንድትኾን ማድረግና የፌዴራል መንግሥት የአማራ ሕዝብ ኅብረ ብሔራዊ እና ልማት ወዳድ እንጅ ጦርነትን የማይፈልግ መኾኑን በውል በመገንዘብ የሕዝቡን ተዘዋውሮ የመሥራት እና … Read moreContinue Reading
- ለወልቃይት ጠገዴ ሴቲት ሁመራ አንድ ሚሊዮን የጉልበት ሰራተኛ ይፈለጋል፤ ከአንድ ነጥን አንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ሰሊጥ ይጠበቃል“ከየትኛውም የኢትዮጵያ ክልል አስተማማኝ ሰላም ያለው እዚህ ነው። ለሰራተኞች እንደ ቤተሰብ ዝግጅት አድርገናል። ኑ” ሲሉ የተሰሙት አምስት መቶና ሶስት መቶ ሄክታር ሰሊጥና ማሽላ ያመረቱ ባለሃብቶች ናቸው። የዞኑ ግብርና ቢሮ ሃላፊ እንዳሉት አንድ ሚሊዮን አንድ መቶ ሃምሳ ሁለት ሺህ ኩንታል የሰሊጥ ምርት ስለሚጠበቅ ከአንድ ሚሊዮን በላይ የሰራተኛ ሃይል ያስፈልጋል። የዞኑ አርባ … Read moreContinue Reading
- የጎንደርን ከተማ ምን አይነት ተኩስ እንደሌለ ተገለጸ፤ ጎንደር ተይዛለች ተብሎ ነበር“ጎንደር ከተማን ሙሉ በሙሉ ይዘናታል” ሲሉ ስማቸው እንዳይገለጽ ጠይቀው ለጀርመን ድምጽ መረጃ በሰጡ የአማራ ሕዝባዊ ኃይል ፋኖ ቃል አቀባይ አየር ማረፊያውን ሆን ብለው እንዳልያዙ አመልክተዋል። እሳቸው ተናገሩ የተባለው በጀርመን ድምጽ እየተሰማ በለበት ሰዓት በተመሳሳይ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ውጊያ መደረጉን ሳያስተባብል ከተማዋን ለመያዝ የገባው ሃይል መደምሰሱን አሃዝ ጠቅሶ አመልክቷል። አገር መከላከያም … Read moreContinue Reading
- “የሞተው ባልሽ ገዳዩ ወንድምሽ፣ሀዘንሽ ቅጥ አጣ ከቤትሽ አልወጣ”የሞተው ባልሽ ገዳዩ ወንድምሽ (ሀዘንሽ ቅጥ አጣ ከቤትሽ አልወጣ) የሚለው የቆየ ተረት ልብን የሚያደማ ኩነትን ማሳያ ነው። እቺ መከረኛ ሚስት ባልዋ በእናቷ ልጅ ወንድሟ ተገደለ። ሟች ባል፣ ገዳይ ወንድም … ኢህአፓ “ሃይማኖት ነው” በሚል ሲገልጸው በነበረው ትግል በቀይና ነጭ ሽብር ስም እናቶች የወላድ መካን ሆነዋል። ጧሪ ያጡና ባዶ ቤት ሃዘን … Read moreContinue Reading