ትናንት ከሀገር ፍቅር እና ደመ ሞቃትነት የተነሳ አንድ ትውልድ በሚባል መልኩ ዋጋ ከፍሏል። ከዚያ መማር የዚህ ትውልድ የቤት ሥራ ነው፡፡ ሀገርን መጠበቅ፣ ሥልጣኔን ማስቀጠል እና ውስብስብ የኾነውን ዓለም ተረድተው መውጫ ብልሃት የሚያመነጩ ልጆችን ኢትዮጵያ ትፈልጋለች ። እኛ ከእኛ የተሻለ ትውልድ መፍጠር ካልቻልን ሀገር እየገደልን ነው” ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
ጳግሜን 5 የትውልድ ቀን ” ኢትዮጵያ የትውልዶች ድምር” በሚል መሪ ሃሳብ በፌዴራል ደረጃ እየተከበረ ነው፡፡ ትምህርት ሚኒስቴር፣ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር እና ፍትሕ ሚኒስቴር በጋራ ባዘጋጁት የትውልድ ቀን በዓል ላይ ፕሬዚዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴን ጨምሮ አርበኞች፣ አረጋዊያን እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
በመርሐ ግብሩ ላይ ተገኝተው ለበዓሉ ታዳሚዎች መልእክት ያስተላለፉት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የአሁኑ ትውልድ ካለፈው የሚማር እና ለሚመጣው የሚያስተምር መደላድል ነው ብለዋል፡፡ በአዲስ ዓመት ዋዜማ ላይ ቆመን ያለፈውን እና የሚመጣውን ስናስብ ለነገ ተስፋ የምናይበት ነው ብለዋል፡፡
ሽግግሩ የአንድ ዓመት ብቻ ሳይኾን በርካታ ዘመናትን አስታውሰን፤ እልፍ ዘመናትን የምንቀበልበት ነው ያሉት ፕሮፌሰር ብርሃኑ የእርሳቸው ትውልድ በርካታ ጥሩ ነገሮች እንዳሉት አንስተው አሁናዊው ትውልድ ሊማርበት የሚገባ በርካታ ጉድለቶች ነበሩበት ብለዋል፡፡ ሀገር ወዳድነት፣ ማንበብ፣ ማሰብና ማንሰላሰል እንዲሁም ምክንያታዊነት የዚያ ዘመን በጎ ጎኖች ነበሩ ብለዋል፡፡
“የእኛ ትውልድ የትግሉ ማዕከል ሀገሩ ነበረች” ያሉት የትምህርት ሚኒስትሩ ነገር ግን ዓለምን የምንመለከትበት መነጽር ጠባብ በመኾኑ በርካታ ዋጋ ከፍለናል ብለዋል፡፡ አንድ ፖለቲካዊ ርዕዮተ ዓለም እንደ መታገያ መስመር መውሰድ እና እርሱን ብቻ መፍትሔ አድርጎ መመልከት ድክመት ነበር፤ የሀገሪቱን ነባራዊ ሁኔታ ከግምት ውስጥ አለማስገባትም ዋጋ አስከፍሏል ብለዋል፡፡
ትናንት ከሀገር ፍቅር እና ደመ ሞቃትነት የተነሳ አንድ ትውልድ በሚባል መልኩ ዋጋ ከፍሏል ያሉት ፕሮፌሰር ብርሃኑ ከዚያ መማር የዚህ ትውልድ የቤት ሥራ ነው ብለዋል፡፡ ሀገርን መጠበቅ፣ ሥልጣኔን ማስቀጠል እና ውስብስብ የኾነውን ዓለም ተረድተው መውጫ ብልሃት የሚያመነጩ ልጆችን ኢትዮጵያ ትፈልጋለች ነው ያሉት፡፡
ሚኒስትሩ በንግግራቸው ላለፉት ሦስት አስርት ዓመታት ትውልዱ የተወዛገበ የሞራል መሰረት ላይ መቆሙን ጠቁመው፤ “እኛ ከእኛ የተሻለ ትውልድ መፍጠር ካልቻልን ሀገር እየገደልን ነው” ብለዋል፡፡ ትምህርት ሚኒስቴር በቅርቡ እየፈጸማቸው ያሉ የሥርዓተ-ትምህርት ማሻሻያ እና የትምህርት ፍኖተ ካርታ ትግበራ ዓላማው ተማሪዎችን መጣል ሳይኾን ራሱን ችሎ የሚቆም ትውልድ ማፍራት እንደኾነ አንስተዋል፡፡
በጎ፣ ግብረ-ገብ፣ አንሰላሳይ፣ አሳቢ፣ ምክንያታዊ እና ትጉህ ተማሪ ለማፍራት ኢትዮጵያዊያን በጋራ እንዲቆሙም ሚኒስትሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ዘጋቢ፡- ታዘብ አራጋው አሚኮ
- ኢትዮጵያ በአሜሪካ የሚኖሩ “ተፈላጊዎች” ተላልፈው እንዲሰጧት ጥያቄ አቀረበችአሜሪካ ተቀምጠው የኢትዮጵያን ሰላም የሚያውኩ ተፈላጊዎችን ሀገሪቱ አሳልፋ በመስጠት ትብብር እንድታደርግ የፌደራል ፖሊስ መጠየቁ ተገለጸ። በጀርመን በተመሳሳይ ስራ መጀመሩ የሚታወስ ነው። ኢትዮጵያ በአሜሪካ የሚኖሩ “ተፈላጊዎች” ተላልፈው እንዲሰጧት… Read more: ኢትዮጵያ በአሜሪካ የሚኖሩ “ተፈላጊዎች” ተላልፈው እንዲሰጧት ጥያቄ አቀረበች
- ሃሰተኛ የተባሉ የዩቲዩበር ባለቤቶች ተያዙ፤ በአንድ ተጠርጣሪ ብቻ ስምንት የዩቲዩብ ቻናል ተከፍቷልፈቃድ ሳይኖራቸው በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስምንት አማረ እና ቤተሰቦቹ በተባለ ህንፃ ላይ ቢሮ ተከራይተው ሃሰተኛና የፈጠራ ወሬ ሲያሰራጩ ነበሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች መያዛቸው ተገለጸ። ተጠርጣሪዎቹ የተያዙት በህዝብ… Read more: ሃሰተኛ የተባሉ የዩቲዩበር ባለቤቶች ተያዙ፤ በአንድ ተጠርጣሪ ብቻ ስምንት የዩቲዩብ ቻናል ተከፍቷል
- “ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋግጠዋል”፤ የሚለው ዜና የአማራ ፖለቲካን ቀየረበሱዳን ለአንድ ዓመት የዘለቀው የእርስ በእርስ እልቂት ብዙ ተዋንያኖች አሉበት። ከአርቡ ዓለም፣ ከአውሮፓ፣ ከአፍሪቃ፣ ሩሲያና አሜሪካንን ጨምሮ የተለያዩ አካላት የሚዳክሩበት በዚህ ጦርነት የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግንባር… Read more: “ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋግጠዋል”፤ የሚለው ዜና የአማራ ፖለቲካን ቀየረ
- Are Tigray mercenaries fighting in conflict-ravaged Sudan?Mercenaries from Ethiopia’s Tigray People’s Liberation Front are fighting alongside Sudanese army regulars against fighters of the Rapid Support Forces (RSF), the paramilitary group is claiming. The… Read more: Are Tigray mercenaries fighting in conflict-ravaged Sudan?
- Sudan’s RSF Accuse Tigray People’s Liberation Front of Backing SAFSudanese warring party Rapid Support Forces has officially accused the Tigray People’s Liberation Front Fighters of fighting in Sudan in support of the Sudanese Armed Forces (SAF).… Read more: Sudan’s RSF Accuse Tigray People’s Liberation Front of Backing SAF