የባህር ዳር ነዋሪዎች የሕዝብን ጥያቄ የመፍታት አቅም፣ ፍላጎት እና ቅንነት ያለው አመራር በመፍጠር ሕዝብን መካስ እንደሚያስፈልግ፣ ኢትዮጵያ በዘር ከመገፋፋት እና ከመጠቃቃት ነጻ የኾነች ፣ዜጎች በሁሉም ቦታ እኩል የሚስተናገዱባት ሀገር እንድትኾን ማድረግና የፌዴራል መንግሥት የአማራ ሕዝብ ኅብረ ብሔራዊ እና ልማት ወዳድ እንጅ ጦርነትን የማይፈልግ መኾኑን በውል በመገንዘብ የሕዝቡን ተዘዋውሮ የመሥራት እና የደኅንነት መብት እንዲያስተብቅ በውይይት መድረክ አነሱ። ጥላቻን የሚያባባሱ ሚዲያዎችንም አውግዘዋል።
ሁለንተናዊ እና ዘላቂ ሰላም ለመገንባት የሁሉንም ርብርብ ይጠይቃል” በሚል መሪ ሀሳብ በባሕርዳር ከተማ ሕዝባዊ ውይይት ተካሂዷል። የባሕርዳር ከተማ አሥተዳደር የግሽ ዓባይ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ተስፋሁን ድረስ በመድረኩ ላይ ተገኝተው የመወያያ ሀሳብ አቅርበዋል። አቶ ተስፋሁን የተፈጠረው ግጭት የክልሉን ሕዝብ ኑሮ ያናጋ በተለይም ደግሞ አርሶ አደሩ ወቅቱን ጠብቆ የማምረት ሥራውን እንዳያከናውን ያስተጓጎለ ነው ብለዋል።
አቶ ተስፋሁን የአማራ ሕዝብ የወሰን እና የማንነት፣ የሕገ መንግሥት፣ በነጻነት ተዘዋውሮ የመሥራት፣ የፍትሐዊነት እና ሌሎችም በርካታ ጥያቄዎች ያሉት ቢኾንም ጦርነትን እንደመፍትሄ መቁጠር ግን ተገቢ አለመኾኑን አስረድተዋል። ይልቁንም ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ጋር በመኾን ጥያቄዎች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ በሆደ-ሰፊነት መታገል ያስፈልጋል ነው ያሉት።
አቶ ተስፋሁን ልዩነት ያላቸው አካላት የክልሉን የሰላም ጥሪ ተቀብለው ወደ ሰላማዊ ንግግር መመለስ አለባቸውም ብለዋል። በፍፁም ሰላማዊነት መነጋገር ሲገባ በትጥቅ የተደገፈ ትግል ውስጥ ተገብቶ የሕዝብን ደኅንነት ማወክ ትክክለኛ አማራጭ አለመኾኑንም ጠቁመዋል።
አሁንም ቢኾን ግጭትን በማስወገድ አላስፈላጊ የሕይወት መስዋዕትነት መቀነስ እና የክልሉን ኢኮኖሚም ከውድመት መታደግ ያስፈልጋል ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። የተከሰተውን ችግር በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ሁሉም ለሰላም ዘብ መቆም እና ተከታታይ ውይይቶችን ማድረግ እንደሚገባም ጠቁመዋል።
ተወያዮች እንዳሉት፦
- የሕዝብን ጥያቄ የመፍታት አቅም፣ ፍላጎት እና ቅንነት ያለው አመራር በመፍጠር ሕዝብን መካስ ያስፈልጋል
- ኢትዮጵያ በዘር ከመገፋፋት እና ከመጠቃቃት ነጻ የኾነች ፣ዜጎች በሁሉም ቦታ እኩል የሚስተናገዱባት ሀገር እንድትኾን ማድረግ ያስፈልጋል።
- የፌዴራል መንግሥት የአማራ ሕዝብ ኅብረ ብሔራዊ እና ልማት ወዳድ እንጅ ጦርነትን የማይፈልግ መኾኑን በውል በመገንዘብ የሕዝቡን ተዘዋውሮ የመሥራት እና የደኅንነት መብት ያስጠብቅ።
- ግጭትን ለማባባስ የሚጥሩ ግለሰቦች እና ሚዲያዎች ለሕዝብ ሰላም ማሰብ እና ከድርጊታቸው መቆጠብ አለባቸው።
- ተቀመጠው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የክልሉን የሰላም ሁኔታ እየገመገመ የሚሻሻል መኾን አለበት።
- ዘላቂ ሰላም እንዲመጣ መንግሥት ጠንካራም ሆደ ሰፊም አመራር መስጠት አለበት።
- የአማራ ሕዝብ ለሀገር መከላከያ ሠራዊት ደጀን በመኾን በኩል በተግባር የተፈተነ ታሪክ ያለው ነው። ከዚህ እውነታ በሚቃረን ሁኔታ ሠራዊቱን ከአማራ ሕዝብ ለመነጠል የሚሠራ አሻጥር በፍጥነት መቆም አለበት ሲሉም የውይይቱ ተሳታፊዎች አንስተዋል።
በውይይቱ ላይ የተገኙት በሀገር መከላከያ ሠራዊት የሰሜን ምዕራብ ዕዝ የሠራዊት ግንባታ ሥራዎች አስተባባሪ ኮሎኔል ተስፋየ ኤፍሬም የሀገር መከላከያ ሠራዊት በሕግ በተቀመጠለት ተልዕኮ መሰረት እና በጥብቅ ሥነ ምግባር የሚንቀሳቀስ ነው ብለዋል። “ሠራዊቱ የሀገርን እና የሕዝብን ሰላም ከማስጠበቅ የዘለለ ሌላ አጀንዳ የለውም” ሲሉም ተናግረዋል። ለሠራዊቱ ደጀን እየኾነ ታሪካዊ ውለታ ሲከፍል የኖረው የአማራ ሕዝብ ሰላሙ በዘላቂነት እንዲከበር በትኩረት እንሠራለንም ብለዋል። የክልሉ ሰላም ተገምግሞ መሻሻል የሚያሳይ ከኾነ የተጣለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሊነሳ እንደሚችልም አመላክተዋል።
ኮሎኔል ተስፋየ “ከግጭት አዙሪት ወጥቶ ወደ ሰላም ከፍታ ለመሻገር የሁላችን ርብርብ እና መደማመጥ ያስፈልጋል” ሲሉም ተናግረዋል። አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎች ወጣቶችን በመምከር ለሀገር ሰላም መቆም እንዳለባቸውም መልእክት አስተላልፈዋል።
- ሰው ሰራሽ ቦይ በመገንባት ቀይ ባህርን መቀላቀል የኢትዮጵያ ሌላ አማራጭ?አርተፊሻል ቦይ በመገንባት ቀይ ባህርን ወደ ኢትዮጵያ በማምጣት ኢትዮጵያ የባህር በር ሊኖራት ይችላል፤ ይህ በአለም ላይ በኢትዮጵያ የአፋር ምድር ረባዳነት የተነሳ ተፈጥሮ የሰጠው እድል ነው! በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል አርተፊሻል ቦይ በመስራት ኢትዮጵያ የወደብ ባለቤት መሆን ትችላለች፡፡ እንደዚህ አይነት አጋጣሚ ሊፈጠር የቻለው፤ የኢትዮጵያ የአፋር ቦታ ከባህር ወለል በታች እስከ 110 … Read moreContinue Reading
- ብሄራዊ ባንክ የገንዘብ ቁጥጥሩን አጠንክሮ እንደሚገፋበት አስታወቀ፤ ህገወጥ የወርቅ አዘዋዋሪዎች ላይ እርምጃ እየተወሰደ ነው– የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አዲስ የማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጅ አዘጋጀ በአገሪቱ የሚታየውን የዋጋ አለመረጋጋት ለመግራት የግንዘብ ስርጭት ላይ ጥብቅ ቁጥጥር በማድረግ የተጀመረው ስራ ውጤት እያሳየ መሆኑ ተመለከተ፤ ተጠናክሮ ክምሩ እንደሚሰራበትና ግሽበትን በዓመቱ መጨረሻ 20 ከመቶ ለማድረስ መታቀዱ ተሰማ። ህገወጥ የወርቅ ነጋዴዎች ላይ ጥብቅ ቁጥጥርና የማበረታቻ መደረጉ ለውጥ ቢያሳይም በቂ እንዳልሆነ ተመለከተ። … Read moreContinue Reading
- የኮሚሽኑ የቀድሞ ሠራተኞች ከ40 ሚሊየን ብር በላይ የሙስና ክስ ጋር ተያይዞ ያቀረቡት የክስ መቃወሚያ ውድቅ ሆነየአዲስ አበባ እሳት እና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የቀድሞ ሠራተኞች ከ40 ሚሊየን ብር በላይ የአልባሳት ግዢ ጋር ተያይዞ በቀረበባቸው የሙስና ወንጀል ክስ ያቀረቡት የክስ መቃወሚያ ውድቅ ተደረገ። ተከሳሾቹ ያቀረቡትን የክስ መቃወሚያ ውድቅ ያደረገው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው። የፍትሕ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ … Read moreContinue Reading
- መንግስት የነዳጅ ድጎማን በህገወጥ መንገድ ሲጠቀሙ ነበሩ ያላቸውን 40 ሺህ ተሽከርካሪዎች ከስርአቱ አስወጣ፣ የሰርቁትን ይከፍላሉየታለመለት የነዳጅ ድጎማን ላልተገባ ዓላማ ሲጠቀሙ የነበሩ 40 ሺህ ተሽከርካሪዎች ከድጎማ ስርዓቱ እንዲወጡና ዕዳ እንዲከፍሉ መደረጉን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዶክተር ፍጹም አሰፋ ገለጹ። ሚኒስትሯ ይህን ያሉት የመንግሥት የ2016 የመጀመሪያ የሩብ ዓመት አፈጻጸም በተገመገመበት ወቅት ነው። የግምገማው ተሳታፊዎች መንግሥት የነዳጅ ድጎማን ጨምሮ በርካታ የህዝብ ተጠቃሚነትን የሚያረጋገጡ ተግባራትን ማከናወኑን አድንቀው፤ ሆኖም” ድጎማው … Read moreContinue Reading
- በዓመት አምስት ሚሊዮን ቶን ሲሚንቶ የሚያመርተው ፋብሪካ ከመጋቢት በሁዋላ የሲሚንቶ ዋጋ ወደ ነበረበት የሚመልሰ ነውበቀን 10 ሺህ ቶን ሲሚንቶ እንዲያመርት እቅድ ተይዞለት በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን እንሳሮ ወረዳ ለሚ ከተማ እየተገነባ ያለውን የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ የግንባታ በመጋቢት ወር ይጠናቀቃል። ምርቱ በተባለው ወር ሲጀምር የሲሚንቶ ዋጋ አሁን ካለበት በግማሽ እንደሚወርድ ይጠበቃል። ከመጋቢት በሁዋላ ፋብሪካው በ50 በመቶ የሲሚንቶ እጥረቱን ያስወግዳል። ኢስት አፍሪካን ሆልዲንግ ኩባንያ … Read moreContinue Reading