« የትግራይን ክልል ከ32 ዓመታት በላይ በበላይነት ሲመራ የቆየው ህወሓት ለሁለት ዓመታት በተካሄደው አውዳሚ ጦርነት ምክንያት ከብዙ የትግራይ ተወላጆች በኩል ከባድ ተቃውሞ እየገጠመው መሆኑ መነገር ከጀመረ ቆይቷል። ከሰላም ስምምነቱ ጎን ለጎን “ለምን አስጨረሰን” በሚል ለሚነሳ ጥያቄና በክልሉ በጥቅሉ እንዲህ ያለ ቀውስ እንዲደርስ የተፍለገበት መነሻ ምን እንደሆነ የሚጠይቁ በርክተዋል የሚል ተደጋጋሚ መረጃ አዘል ጽሁፎችና አስተያየቶች እንደሚሰሙ ቢቢሲን ጨምሮ በርካታ የትህነግ የቀድሞ ደጋፊ የነበሩ ዘግበዋል።
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታቸው ረዳ አቶ ዓለም ገብረዋህድን ጨምሮ አራት ከፍተኛ አመራሮችን ከሥልጣን ማንሳታቸው ተስመቷል። ይህ የሆነው ባለፉት ሳምንታት አቶ ጌታቸውን ገምግሞ ከስልጣን ለማስወገድ ያለመ የትህነግ ካድሬዎች ስብሰባ መጠራቱን ተከትሎ ነው።
ከትህነግ ሰፈር መረጃ የሚያገኘው ቢቢሲ እነ ዶክተር ደብረጽዮንና ዓለም ገብረዋህድ የጠሩት ስብሰባ አቶ ጌታቸው የሚመሩትን ካቢኔ የማስወገድ ዓላማ እንደነበረው ዘግቧል። አሁንም የባለስልታናቱን መነሳት አስመልክቶ የሚከተለውን አስፍሯል።
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ በህወሓት እና በክልሉ ውስጥ ከፍተኛ ሚና አላቸው የሚባሉትን አቶ ዓለም ገብረዋህድን ጨምሮ አራት የጊዜያዊ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ከሥልጣን አነሱ።
ከሥልጣናቸው ከተነሱት መካከል በምክትል ፕሬዝዳንትነት ማዕረግ የትግራይ ክልል የጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት የሕዝብ አደረጃጀት አማካሪ የሆኑት አቶ ዓለም ገብረዋህድ ይገኙበታል።
አቶ ጌታቸው ከሥልጣናቸው ካነሷቸው አመራሮች መካከል የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ የነበሩት አማኑኤል አሰፋ፣ የደቡብ ምሥራቅ ዞን አስተዳዳሪ ሊያ ካሳ እንዲሁም የሰሜን ምዕራብ ዞን አስተዳዳሪ ተክላይ ገ/መድኅን ይገኙበታል።
የአቶ ጌታቸው ረዳ ፊርማ ያረፈበት ደብዳቤ ኃላፊዎቹ ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምሥጋና በመግለጽ ከጥቅምት 14 እና 15/2016 ዓ.ም. ጀምሮ ከኃላፊነታቸው መነሳታቸውን ገልጿል።
አቶ ዓለም ገብረዋህድ የህወሓት ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል እና የፓርቲው የጽ/ቤት ኃላፊ ሲሆኑ፣ አማኑኤል አሰፋ፣ ሊያ ካሳ እና ተክላይ ገ/መድኅን ደግሞ የህወሓት የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ናቸው።
ለአራቱ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ከኃላፊነት መነሳት ምክንያት ምን እንደሆነ በጊዜያዊ አስተዳደሩ በኩል የተሰጠ ማብራሪያ የለም።
በክልሉ ዋነኛ ፓርቲ የሆነው ህወሓት ከፍተኛ አመራሮቹ ከጊዜያዊ አስተዳደሩ እንዲወጡ መደረጋቸውን በተመለከተ እስካሁን ያለው ነገር የለም።
አቶ ጌታቸው ባለፉት ሳምንታት የተለያዩ ኃላፊዎችን ከሥልጣን ሲያነሱ የአሁኑ የመጀመሪያቸው አይደለም። ከሳምንት በፊት የህወሓት ከፍተኛ አመራሮች ከጠሩት እና ጊዜያዊ አስተዳደሩ ከተቃወመው ስብሰባ ጋር በተያያዘ የዞን ባለሥልጣናትን ማሰናበታቸው ይታወቃል።
ከተመሠረተ ወራት ባስቆጠረው በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር እና በህወሓት መካከል የተፈጠረው ልዩነት በግልጽ ወጥቶ ባይነገርም ባለፉት ቀናት ልዩነቱ በይፋ መታየት ጀምሯል።
ከሳምንት በፊት የህወሓት አመራሮች የጠሩትን የካድሬዎች ስብሰባ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት “ያለ እውቅና የተጠራ ነው” በማለት እንዳይካሄድ መወሰናቸው ይታወሳል።
ይህ በህወሓት ከፍተኛ አመራሮች መካከል የሃሳብ ልዩነት ያስከተለ ሲሆን፣ የፓርቲው ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል እና የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት ስብሰባው እንዳይካሄድ የወሰዱትን እርምጃ “ተቋማዊ አሠራርን ያልተከተለ ነው” ሲል ፓርቲው ተችቶታል።
የፌደራል መንግሥቱ እና ህወሓት ለሁለት ዓመታት የቆየውን ደም አፋሳሽ ጦርነት ያስቆመውን የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት ከተፈራረሙ በኋላ ጌታቸው ረዳ ክልሉን በጊዜያዊነት እንዲያስተዳደሩ በጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ መሾማቸው ይታወሳል።
አቶ ጌታቸው ጊዜያዊ አስተዳደራቸው ዘጠኝ ወራትን ቢያስቆጥርም፣ በትግራይ ክልል ባሉ ዞኖች እና ወረዳዎች መዋቅሩን መዘርጋት አለመቻሉን ተናግረው ነበር።
የአቶ ጌታቸው ጊዜያዊ አስተዳደር ባለፉት ወራት የሚጠበቅበትን ሥራ ለማከናወን እንቅፋቶች እንደነበሩበት የገለጸ ሲሆን፣ እራሳቸውም አስተዳደራቸው በዞኖች እና በወረዳዎች ውስጥ እግሩን መትከል አለመቻሉን እና አንዳንድ ወረዳዎች የጊዜያዊ አስተዳደሩ አካል መሆናቸውን እንዳይቀበሉ የሚያደርግ “የተደራጀ እንቅስቃሴ” መኖሩን ተናገረው ነበር።
አቶ ጌታቸው አባል የሆኑበት እና በዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል የሚመራው ህወሓት ከአንድ ሳምንት በፊት በጠራው ስብሰባ ላይ የአቶ ጌታቸው ጊዜያዊ አስተዳደርን ዋነኛ አጀንዳ ለማድረግ ታስቦ እንደነበር ለደኅንነታቸው ሲሉ ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ ውስጥ አዋቂ ለቢቢሲ መናገራቸው ይታወሳል።
“የተጠራው የካድሬዎች ስብሰባ የጊዜያዊ አስተዳደሩን እና በተለይም የአቶ ጌታቸው ረዳን አመራር ለመገምገም ያነጣጠረ እና ህወሓት የጊዜያዊ አስተዳደሩን ሥልጣን ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር ያለመ ነበር” ብለዋል።
የትግራይን ከ32 ዓመታት በላይ በበላይነት ሲመራ የቆየው ህወሓት ለሁለት ዓመታት በተካሄደው አውዳሚ ጦርነት ምክንያት ከብዙ የትግራይ ተወላጆች በኩል ከባድ ተቃውሞ እየገጠመው መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧል።
- በትግራይ የጊዚያዊ አስተዳደሩና የትህነግ አለመግባባት ከፍተኛ ስጋት ፈጥሯል – ጎራ የለየ ግጭት?በትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደርና በህወሐት መካከል ያለው የስላጣን ሽኩቻ ተካሮ አንዱ በአንዱ ላይ የስም ማጥፋት ዘመቻው በግላጭ እየተካሄደ ከመሆኑም አልፎ ጎራ ለይተው እስከመገዳደል እንዳይደረስና የተገኘው አንጻራዊ ሰላም… Read more: በትግራይ የጊዚያዊ አስተዳደሩና የትህነግ አለመግባባት ከፍተኛ ስጋት ፈጥሯል – ጎራ የለየ ግጭት?
- የአባይ ድልድይ ተመረቀ፤ ፋኖ ኢላማውን የጠበቀ ጥቃት ሰነዘርኩ አለ፤ አብይ አሕመድ “መገዳደል ይብቃ” አሉበተመረጡ ቦታዎች፣ የግልና የመንግስት ተቋማት ላይ ቦንብ ማፈንዳቱን ፋኖ አስታወቀ። ይህን ያስታወቀው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ የአባይ ድልድይን ለመመረቅ ወደ ባህር ዳር እንዳይመጡ ለ”ቅድሚያ ማስጠንቀቂያ” በሚል… Read more: የአባይ ድልድይ ተመረቀ፤ ፋኖ ኢላማውን የጠበቀ ጥቃት ሰነዘርኩ አለ፤ አብይ አሕመድ “መገዳደል ይብቃ” አሉ
- ኢትዮጵያ በአሜሪካ የሚኖሩ “ተፈላጊዎች” ተላልፈው እንዲሰጧት ጥያቄ አቀረበችአሜሪካ ተቀምጠው የኢትዮጵያን ሰላም የሚያውኩ ተፈላጊዎችን ሀገሪቱ አሳልፋ በመስጠት ትብብር እንድታደርግ የፌደራል ፖሊስ መጠየቁ ተገለጸ። በጀርመን በተመሳሳይ ስራ መጀመሩ የሚታወስ ነው። ኢትዮጵያ በአሜሪካ የሚኖሩ “ተፈላጊዎች” ተላልፈው… Read more: ኢትዮጵያ በአሜሪካ የሚኖሩ “ተፈላጊዎች” ተላልፈው እንዲሰጧት ጥያቄ አቀረበች
- ሃሰተኛ የተባሉ የዩቲዩበር ባለቤቶች ተያዙ፤ በአንድ ተጠርጣሪ ብቻ ስምንት የዩቲዩብ ቻናል ተከፍቷልፈቃድ ሳይኖራቸው በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስምንት አማረ እና ቤተሰቦቹ በተባለ ህንፃ ላይ ቢሮ ተከራይተው ሃሰተኛና የፈጠራ ወሬ ሲያሰራጩ ነበሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች መያዛቸው ተገለጸ። ተጠርጣሪዎቹ የተያዙት… Read more: ሃሰተኛ የተባሉ የዩቲዩበር ባለቤቶች ተያዙ፤ በአንድ ተጠርጣሪ ብቻ ስምንት የዩቲዩብ ቻናል ተከፍቷል
- “ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋግጠዋል”፤ የሚለው ዜና የአማራ ፖለቲካን ቀየረበሱዳን ለአንድ ዓመት የዘለቀው የእርስ በእርስ እልቂት ብዙ ተዋንያኖች አሉበት። ከአርቡ ዓለም፣ ከአውሮፓ፣ ከአፍሪቃ፣ ሩሲያና አሜሪካንን ጨምሮ የተለያዩ አካላት የሚዳክሩበት በዚህ ጦርነት የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ… Read more: “ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋግጠዋል”፤ የሚለው ዜና የአማራ ፖለቲካን ቀየረ