Site icon ETHIO12.COM

ወቅታዊውን የሱዳን መሬት ወረራ በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በፓርላማ የተናገሩት‼

👉 ሱዳንን በሚመለከት በዲፕሎማስው ሰፊ ስራ እየሰራን ነው፡፡ ከሱዳን ጋር ጦርነት መጀመር አያስፈልግም ኪሳራ ነው ፤

👉 ሱዳንም አሁን ባለው ሁኔታ ከጎረቤት አገር ጋር ለመዋጋት በሚያስችል ቁመና ላይ አይደለም ያለችው ፡፡ብዙ የውስጥ ችግር አለባት፤

👉 ኢትዮጵያም አሁን ባለው ሁኔታ ከሱዳን ጋር ለመዋጋት ብዙ ችግር አለባት፤ ስለዚህ ጦርነቱ ለሁለታችንም አያስፈልገንም፤

👉 ችግሩን በንግግር፣ በውይይት፣ በድርድር መፍታት ነው የሚያስፈልገው፤ ያ ተጀምሯል፤

👉 ከአጼ ሚኒሊክ ዘመን ጊዜ ጀምሮ እስከአሁን ድረስ በንግግር ያለጉዳይ ነው፤ በእኛ በኩል በምክትል ጠቅላይ ሚንስትሩ የሚመራ ኮሚቴ በእነሱ በኩልም በሚንስትር የሚመራ ኮሚቴ ተቋቁሞ እየተሰራበት ነው፤

👉 ላለፈው አንድ አመት ያህል ስራ ስንሰራ ቆይተናል፤ አሁን ይሄ የሕግ ማስከበሩ ስራ ሲጀመር ነው የተቋረጠው፡፡ በዚህ ወቅት እነሱ ወደማይገባ መንገድ ሄዱ፤

👉 እኛ ለዚህ የሰጠነው ምላሽ በሁለቱ ሕዝቦች መካከል ውጊያ አያስፈልግም፤ በውይይትና በድርድር እንፍታው ነው ያልነው፤

👉 ይሄን ስንልም የእኛ አርሶ አደሮች ተፈናቅለዋል፤ ማሳቸው ተቃጥሏል፤ ቤታቸው ተቃጥሏል፤ በደል ደርሶብናል፤ ያም ሆኖ አንዋጋ እያልን ነው፤ ውጊያ ስለማይጠቅመን፤

👉 ይሄ እንደተጠበቀ ሆኖ ሱዳን ከሌሎች ጋ ወዳጅነት ፈጠረች የተባለው ሱዳን ከማንኛውም አገር ጋ ወዳጅ መሆን ትችላለች፤ የኢትዮጵያ ጠላት መሆን ግን አትችልም፤

👉 ሱዳን የሚለው ቃል በአርብኛ እና ኢትዮጵያ የሚለው ቃል በግሪክኛ አንድ ነው ትርጉሙ፤ አንድ ሕዝብ ነው፤ የትም አገር ሄዳችሁ ሱዳናዊ ብታዩ በአማርኛ ነው የምታወሩት፤

👉 ኢትዮጵያን ከሱዳን መለየት አይቻልም፤ ከማንኛውም አገር ጋ ወዳጅ መሆን ይቻላል፤ ችግር የለውም፡፤ እኛም ከሌሎች አገራት ጋር ወዳጅ መሆን እንችላለን፤ የሱዳን ጠላት መሆን ግን አንችልም፤

👉 በብዙ ነገር አንድ ሕዝቦች ነን፤ ተከባብረንና ተዋድደን የኖርን ወደፊትም አብረን የምንኖር ሕዝቦች ነን፤

Exit mobile version