ወደ አማራ ክልልና ትግራይ በመግባት ሁለቱም አካላት ለትግራይ ስጋት በማይሆኑበት ደረጃ እስኪደርሱ ጥቃት እንደሚሰነዝር ሲያስፈርራራ የነበረው የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር ትህነግ ባስቸኳይና ሙሉ በሙሉ ተኩስ እንዲያቆም ታዘዘ። ግንባሩ ጥቃት ለማድረስ በዛተው መሰረት በማድመ ሽራሮና ኮረም ጥቃት ለመክሰት ሞክሮ የፈለገው እንዳልሆነለት ተገለጸ።
የተባባሩት መንግሥታት ድርጅት ጸጥታው ምክር ቤት “በአስቸኳይ እና ሙሉ በሙሉ” ሲል ትህነግ የተኩስ አቁም እንዲያደርግ ያሳሰበ በይፋ የትግራይን ጉዳይ አንስቶ በተወያየበት ወቅት ነው።
የድርጅቱ የፖለቲካ ጉዳዮች ኃላፊ ሮዝመሪ ዲካርሎ ተጨማሪ ችግር ሊፈጠር እንደሚችል ስጋታቸውን አኑረዋል። አያይዘውም የተካረረ ግጭት ሊነሳ የሚችልበት ሁኔታ አለ።ይህ ደግሞ አሁን ያለውን የጸጥታ አግባ በቅጽበት ወደ ቀውስ ኪቀይረው እንደሚችል አስረድተዋል። ሃላፊዋ ስጋታቸውን ከዘረዘሩ በሁዋላ ነው “የትግራይ መከላከያ ኃይል የተኩስ አቁም ስምምነቱን በአፋጣኝ እና ሙሉ በሙሉ እንዲያጸድቅ እንጠይቃለን” ሲሉ የተደመጡት። ይህን ተከትሎ የትህነግ ሃላፊዎች በይፋ ምን እንደመለሱ አልታወቀም።
ይህን በሚልበት ወቅት አቶ ጌታቸው በተመድ ተሽከርካሪ ሲንቀሳቀሱ የሚያሳዩ ምስሎች በራሱ በተባበሩት መንግስታት የምግብ ድርጅት አስተባባሪ ሲሰራጭ ነበር። ተመድ በቀውስ ቀጠና ውስጥ ገለልተኛ ሆኖ የሚሰራ፣ ያለመነካት መብት ያለው፣ የህግ ከለላው የተጠበቀ ተቋም ሆኖ ሳለ በዚህ መልኩ አንድ ሉዓላዊ አገር ‘ሽብረተኛ” ያለችውን አካል ከላይ በተሰጠው ያለመነካት መብት ጥላ ስር አድርጎ አገልግሎት መስጠት አግባብ እንዳልሆነ፣ ተቋማቱ ገለልተኛ አለመሆናቸውን የሚያሳይ፣ ለወገንተኛነታቸው ገሃድ መውጣት ምስክር እንደሆነ በስፋት በየአቅጣጫው ሲገልጽ ነበር።
ተመድ ከመርሁ በሚጻረር መልኩ እንዲህ ባለ ተራ ተግባር ውስጥ ተነክሮ ከስፍራው የኢትዮጵያን መንግስት የሚደበድብ ሪፖርት ከስፍራው ሲደርሰው የሚያትምና እውነት ነው ብሎ ዓለም እንዲስት የራሱን ሚና የሚጫወት መሆኑ በበርካቶች በቲዊት እየተነቀፈ ነው።
ትህነግ የተኩስ አቁም እንዲያደርግ መታዘዙ ይፋ ከመሆኑ በፊት በኮረም ትንኮሳ አድርጎ እንደነበር አቶ ሬድዋን አስታውቀዋል። የኦቻ ሪፖርት ደግሞ ባድመና ሽራሮ ብሎ ባይጠቅስም ውጊያ እንደነበር ማስታወቁ አይዘነጋም።ኤርትራ ይህን አስመልክቶ ያለችው ነገር የለም። የአማራ ክልል ግን ትንኮሳውን እንዳመከነ ተመልክቷል። ከዚያም በላይ ክልሉ የትህነግ ሃይል በጦርነት ምንም ነገር ለማድረግ ከሞከር አጻፋ ለመመለስ በቂ ዝግትና ቁርጠኛነት እንዳለ አመልክቷል።
በተያያዘ ሌላ ዜና የአማራ ልዩ ሃይል አከባቢ ለቅቆ እንደማይወጣ በተባበሩት የኢትዮጵያ አምባሳደር በይፋ አመልክተዋል። በተባበሩት መንግስታት የፕሬስ ኮንፍራንስ ስለወልቃይት ጉዳይ ” የአማራ ሃይል ከምዕራብ ትግራይ” እንደሚወጣ የተጠየቁት በተባበሩት መንግስታት አምባሳደር ታዬ ስለአካባቢው ከፖለቲካው በላይ በቂ እውቀት እንዳላቸው ለማመላከት እንደ አጋጣሚ በእናታቸው ወገን የወልቃይት አከባቢ ተወላጅ መሆናቸውን አመልክተዋል።
ደጋግማ ለወተወተቻቸው ጠያቂ “አከባቢው በትግራይ ክልል ስር የተጠቃለለው ህወሓት ወደ ስልጣን ከመጣ በኋላ ነው። ይህም የሆነው ያለ ምንም ህጋዊ መሠረት እና የህዝብ ፍቃድ ነው። በመሆኑም የአከባቢው ነዋሪዎች ያነሱት የማንነት እና የወሰን ጥያቄ በህጋዊ መንገድ መፍትሄ እስከሚሰጠው ድረስ የአማራ ልዩ ሃይል ሆነ የመከላከያ ሰራዊት ከወልቃይት አከባቢ ለቅቆ አይወጣም። ይኸው ነው” ብለዋል። አምባሳደሩ ለጸጥታው ምክር ቤት የተዋጣለት ንግግር ማድረጋቸው በርካቶችን አስደስቷል።
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ ወገኖች… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ። ለውጭ… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት
- የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡምየፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የትራንስፖርት ስምሪትና የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር ሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ 11 ግለሰቦች በስር ፍ/ቤት የተሰጠውን… Read more: የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡም
- መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለየአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ ምክንያቱም “የኢትዮጵያ መንግሥት በሕገ ወጥ መንገድ የአውሮፓ ኅብረት አገራት… Read more: መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ
- “ሰራ ሰራ አድርጌ ቶሎ እመለሳለሁ” ሚሊየነሩ የሸኔ የ”ነጻነት” ታጋይ ወደ ጫካ ሲገባ ስንብት ላይ የተናገረውየሚነሳው ጉዳዩ ልብ ሰባሪ ነው፣ ያስቃል፣ ያዝናናል፣ ያስገርማል፣ ያሳዝናል፣ ይቀፋል፣ ያሳፍራል፣ ለማመን ያስቸግራል … አንባቢ ስም ይስጠው።… Read more: “ሰራ ሰራ አድርጌ ቶሎ እመለሳለሁ” ሚሊየነሩ የሸኔ የ”ነጻነት” ታጋይ ወደ ጫካ ሲገባ ስንብት ላይ የተናገረው