ጅቡቲ አንድም ወታደር ወደ ኢትዮጵያ ድንበር እንዳላስጠጋች የፋይናንስና ኢኮኖሚ ሚኒስትሩ አስታወቁ። ሚኒስትሩ ይን ያሉት ራሺድ አብዲ የሚባሉት የምስራቅ አፍሪቃ ተንታኝ “ጅቡቲ በከፍተኛ ደረጃ የታጠቀ ጦሯን ከኢትዮጵያ ጋር ወደሚያዋስናት ድንበር አሰማርታለች” በሚል ላሰራጩት ዜና ዚመልሱ
“ምንጭዎን አልቀበልም” ያሉት Ilyas Dawaleh ሊያስ ዳዋለህ ” አንድም ወታደርም ሆነ የትኛውም የታጠቀ ሃይል ወደ ድንበር እንዳልተሰማራም” የሚል መልስ ብበቲውተር ገጻቸው አስፍረዋል። ” ይህንን ላረጋግጥልዎት እችላለሁ” ሲሉ አስረግጠው ሚኒስትሩ ነግረዋቸዋል። ” ይህን እንድናስብና ጦር እንድናሰማራ የሚያደርገን አንዳችም አደጋ አላጋጠመንም” ሲሉም አክለው ለ” ተንታኙ ቲዊት ምላሽ ሰጥተዋል። በሌላ አነጋገር ” አትቀደድ” ብለዋቸዋል።
የምስራቅ አፍሪቃ አጥኚ፣ ተመራማሪ፣ የፖለቲካ አዋቂ እንደሆኑ በገለ ታሪካቸው ያስቀመጡት ራሺድ አብዲ 136.4 ሺህ ተከታታይ ባላቸው የቲውተር አምዳቸው ላይ ” ጅቡቲ የታጠቁ ወታደሮቿን ከኢትዮጵያ ጋር ወደሚያዋስናት ድንበር አሰማርታለች” ሲሉ የጀምራሉ። አያይዘውም ” ከኢትዮጵያ ጋር የሚያገናኘውን የባቡርና የአውቶሞቢል መንገድ ለመከላከል ጅቡቲ ሃይሏን አስፍራለች” ብለዋል። ዘጠና አምስት በመቶ ኢትዮጵያ በጅቡቲ ወደብ አማካይነት እቃዎችን ወደ አገር ቤት እንደምታስገባ አውስተው ” የትህነግ ሃይል አሁን አፋር ውስጥ ነው። ቡድኑ የትራንስፖርት መስመሩን ሊቆርተው ይችላል” የሚል ሟርት ጽፈው ነበር።
እሳቸው ብቻ ሳይሆኑ ሮይተርስን ጨምሮ በርካታ የውጭ ሚዲያዎችና የተገዙ ኢትዮጵያዊያንም ይህንኑ ሟርት ሲያስተጋቡ ነበር። የጅቡቲው የፋይናንስና ኢኮኖሚ ሚኒስትር ” ምንጭህን ተወውና” ሲሉ ጅቡቲ ወታደር ሰማንቀሳቀስ ጭራሽ አለማሰቧን ያስረዱት።
ትህነግ በያዘው እቅድ መሰረት የጅቡቲን መንገድ በዚህ ሳምንት በቁጥጥር ስር በማድረግ የመደራደሪያ አቅም ለማስፋት ታስቦ እንደንበር ደጋፊዎቻቸው በስፋት ሲናገሩ ነበር። ይሁን እንጂ ዛሬ መከላከያ ዛሬ በሰተው መግለቻ አፋር ዘልቆ የነበረው የትህነግ ሃይል ሙሉ በሙሉ መደምሰሱ አስትውቋል። የትህነግ አመራሮችም አላስተባበሉም።
የአማራ ክልል ኮሙኒኬጭን ቢሮ በበኩሉ አላማጣና ቆቦን እንደያዘ አድርጎ አሸባሪው ቡድን የሚያወራው ሃሰት መሆኑንን ቢያንስ ነዋሪዎች ይታዘባሉ ሲል የክልሉ ሚሊሻና ልዩ ሃይል ድል ማስመዝገቡንና ጥቃቱ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። መከላከያ በበኩሉ ትንኮሳ ሲኖር እርምጃ እንደሚወስድ፣ ከዚህ ውጪ መንግስት ሲወስን ሙሉ ማጥቃት የማድረግ አቅምና ዝግጁነት እንዳለው ይፋ አድርጓል።
የኢትዮጵያ አየር ሃይልም በበኩሉ ከመቼውም ጊዜ በላይ ማናቸውንም ጥቃት ለመዘንዘር ዝግጅቱ እንዳለውና የመንግስትን ትእዛዝ ብቻ እንደሚተብቅ አመልክቷል። ይህ በንዲህ እንዳለ የአፋር ኮሙኒኪሽን ቢሮና የአፋር ልዩ ሃይል በበኩላቸው በርካታ ሕሳናት መማረካቸውን አመልክተዋል። ምስክሮች እንደሚሉት ከሆነ አፋር ክልል ዘልቆ የገባው የትህነግ ሃይል በሄሊኮፕተር በተደረገ ዘመቻ ክፉኛ መጎዳቱ ታውቋል።
በሌላ ዜና አንቶኒ ብሊንከን የወቅቱን የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር በስክል ስለ ትግራይና አባይ ግድብብ ጉዳይ ማነጋገራቸውን መስሪያ ቤታቸው አስታውቋል። መግለጫው ዝርዝር የውይይቱን ሃሳብ በጥልቅ ባይዘረዝርም አፍሪካ ሕዝብረት ኢትዮጵያ ላይ ጫና እንዲያድረግ የተጀመረው ዘመቻ አካል መሆኑን ያመላክታል።
- ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናውቤት የተባለች አንዲት ሴት እንዲህ ብላለች፦ “ደም ማነስ የያዘኝ በአሥራዎቹ ዕድሜ ሳለሁ ነው። ቶሎ ይደክመኝ፣ አጥንቶቼን ይቆረጥመኝ፣ እንዲሁም ትኩረቴ በቀላሉ ይከፋፈል ነበር። ሐኪሜ የብረት… Read more: ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናው
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ ወገኖች አስታውቀዋል። ጎን ለጎን የትግራይ ከፍተኛ ባለስልጣናትና የዞን… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ። ለውጭ አገር ሚዲያዎች ዜና የሚያቀብሉና እነሱኑ የሚከተሉ ስምምነቱ… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት
- የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡምየፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የትራንስፖርት ስምሪትና የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር ሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ 11 ግለሰቦች በስር ፍ/ቤት የተሰጠውን ዋስትና አፀና። ፍርድ ቤቱ ተጠርጣሪዎቹ ከሀገር እንዳይወጡ… Read more: የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡም
- መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለየአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ ምክንያቱም “የኢትዮጵያ መንግሥት በሕገ ወጥ መንገድ የአውሮፓ ኅብረት አገራት ውስጥ የሚኖሩ ዜጎቹን መልሶ ለመቀበል ያሳየው ተባባሪነት… Read more: መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ