የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር “ትህነግ የኢትዮጵያና ኤርትራ የጋራ ጠላት!” እንደሆነ በለውጡ ማግስት በሰፊ ትንተና ያስረዱትና ስጋታቸውን ያሰፈሩት ብሮንዊን ብሩተን፣ አሁን ያለውን ሁኔታ ሲገልጹ የጀመሩት “ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ ኢትዮጵያን ከፍተኛ በሚባል ደረጃ ረግጦ ሲመራ የቆየው ትህነግ” በሚል ነው። ይኸው ድርጅት “አሁን ላይ ለትግራይ ክልል የሚደረጉ የሰብአዊ ድጋፍ ስራዎችን በማደናቀፍ ድጋፍ እንዳይደርስ እያደረገ ነው” ሲሉ ተጠያቂ የሚያደርጉት የአትላንቲክ ካውንስል የአፍሪካ ማዕከል ምክትል ዳይሬክትር ብሮንዊን ብሩተን ናቸው።
ብሮንዊን ብሩተን የስሰብዓዊ ድጋፍ ወደ ትግራይ እንዳይገባ መንገድ መዘጋቱን አስመልክቶ ከቢቢሲ ዜና ክፍለ ጊዜ ጋር ባደረጉት ቆይታ “በክልሉ አሁን ላይ የሰብአዊ ድጋፍ መስተጓጎል እንዲገጥም ያደረገው አሸባሪው ህወሓት ነው” ሲሉ ድርጅቱን በስም “አሸባሪ” ብለው ተጠያቂ አድርገዋል። የኢትዮጵያ መንግስት ያወጀውን የተናጠል ተኩስ አቁም ባለመቀበል አሸባሪው ድርጅት ውጊያ ላይ እንደሚገኝ አስረግጠው ተናግረዋል። ለትግራይ ክልል የሚደረገውን የሰብዓዊ ድጋፍ እንዳይጓጓዝ እያደናቀፈ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
ምክትል ዳይሬክተሯ ዓለም ጆሮ የነፈገውን ጉዳይም አንስተዋል። “አጎራባች አማራና አፋር ክልሎች ላይ ድርጅቱ ባደረገው ጥቃት ዜጎች ተፈናቅለዋል” ሲሉ ከሰዋል። ትህነግ ” ከአማራ ጋር የማወራርደው ሂሳብ አለ” ሲል በለኮሰው ጦርነት ከ200 ሺህ በላይ ሰላማዊ ሰዎች ተፈናቅለዋል። በአፋር በኩል የጅቡቲን መንገድ ለመዝጋት አቅዶ ባደረገው ወረራ ከ100 ሺህ ሰው በላይ ሰላማዊ ነዋሪዎች መፈናቀላቸው የየክልሉ ሃላፊዎች ማስታወቃቸው ይታወሳል። ብሩተን በቁጥር ባይገልጹም ትህነግ የተኩስ አቁም ከተባለ በሁዋላ እያደረሰ ያለውን ጥፋት በይፋ በመቃወም ግንባር ቀደም ሆነዋል
Ethiopia and Eritrea Have a Common Enemy
Abiy Ahmed and Isaias Afwerki are racing toward peace because they both face the same threat: hard-liners in the Tigrayan People’s Liberation Front.
ከቢቢሲ ጋር ቃለ ምልልስ ከማድረጋቸው አስቀድመው ” የኢትዮጵያ መንግስት እርዳታ እንዳይተላለፍ ዘጋ የምትሉ እስኪ አስረዱኝ” ሲሉ የግርምት ጥያቄ በማንሳት በቲውተር ገጻቸው አኑረው ነበር። በአትላንቲክ ካውንስል የአፍሪካ ማዕከል ምክትል ዳይሬክተር የሆኑት ብሮንዊን ብሩቶን ” ዓቢይ አሕመድ የህወሓትን የበላይነት ማሳሳቱን ቀጥሎበታል። እንደ ሳሞራና ጌታቸው ያሉትን አደገኛና ጨካኝ ሰዎችን ከሥራ እንዲለቁ በማድረግ የሚደረገው ተሃድሶ በቀላሉ ሰዎቹ እንዲተኑ አያደርጋቸውም። ከዚህ ሌላ 95በመቶ ትግሬ የሆኑትን ጄኔራሎች በሙሉ ማባረር ለዓቢይ አዋጭ አይደለም። ስለዚህ የሥልጣኑን መንበር ለማጠናከር አደገኛና ጨካኝ የተባሉትን ማባረር፤ አብረውት ለመሥራት የሚፈልጉትን በማስተባበር ዓመታትን መዝለቅ የግድ ይሆንበታል” ሲሉ “ህወሓት፤ የኢትዮጵያና ኤርትራ የጋራ ጠላት!” በሚል ርዕስ ስር ባቀረቡት ጽሁፋቸው አስቀድመው ስጋታቸውን አኑረው ነበር። ሙሉውን ለምንበብ ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ
በቃለ ምልልሳቸው ሽብርተኛው ህወሃት ላለፉት 30 አመታት ገደማ አገሪቷን በአምባገነንነት መግዛቱን ገልጸው፤ የለውጡ ሂደት ከመጣ በኋላ ህወሃት የትግራይ ክልል በማስተዳደር የጦርነት ቅስቀሳ ሲያደርግ ቆይቶ ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም በመከላከያ ሠራዊቱ ላይ ጥቃት መሰንዘሩን አብራርተዋል። በተጨማሪም ሽብርተኛው ቡድን ጥቃቱን በማጠናከር በድጋሚ ወደ ስልጣን ለመምጣት ጦርነት መጀመሩን አመልክተው የፌደራል መንግስትም ይህንን ተከትሎ ወደ ሕግ ማስከበር ዘመቻ መግባቱን መግለፃቸውን አመልክተዋል። በአሸባሪው ቡድን አገዛዝ ምክንያት ከሁለት አስርታት በላይ ኢትዮጵያውያን በከፍተኛ ጭቆና፣ በፍርሃትና በማንነታቸው ጥቃት ውስጥ እንደነበሩ ምክትል ዳይሬክተሯ አመልክተዋል።
- Ethiopia Working To Secure New Development Bank MembershipThe Ministry of Foreign Affairs disclosed that Ethiopia is working hard to become member of BRICS’… Read more: Ethiopia Working To Secure New Development Bank Membership
- National Dialogue, Transitional Justice And Rehabilitation Process Pillars of Lasting Peace, Prosperity: CouncilThe Ethiopian National Security Council has issued a statement on latest developments in the country. In… Read more: National Dialogue, Transitional Justice And Rehabilitation Process Pillars of Lasting Peace, Prosperity: Council
- Somaliland offended by G7 referring the Republic of Somaliland as “Somaliland Region of Somalia”The Republic of Somaliland, is a sovereign state with its own laws and constitution, reaffirmed by… Read more: Somaliland offended by G7 referring the Republic of Somaliland as “Somaliland Region of Somalia”
- Foreign firms’ local market involvement entails economic dynamismPermitting foreign firm’s involvement in the import, wholesale and retail business, which was restricted to local… Read more: Foreign firms’ local market involvement entails economic dynamism
- Kenya’s military chief dies in a helicopter crash, Nairobi declares three days of national mourningKenya’s military chief Gen. Francis Ogolla died in a helicopter crash west of the country, President… Read more: Kenya’s military chief dies in a helicopter crash, Nairobi declares three days of national mourning