“ህወሃት ሰብዓዊ ድጋፎችን ለጦርነት የማዋል ልምድ ያለው ድርጅት ነው፤ በአሁኑ ወቅትም ተመሳሳይ ድርጊት እየፈጸመ ይገኛል” – ጋዜጠኛ አልስቴር ቶምሰን
“ህወሃት ሰብዓዊ ድጋፎችን ለጦርነት የማዋል ልምድ ያለው ድርጅት ነው፤ በአሁኑ ወቅትም ተመሳሳይ ድርጊት እየፈጸመ ይገኛል” ሲል ዓለም አቀፉ ጋዜጠኛ አልስቴር ቶምሰን ተናገረ ፡፡
ከዚህ አኳያ ወደ ትግራይ ክልል እየገባ የሚገኘው እርዳታ ለህብረተሰቡ እየደረሰ አለመሆኑን የሚያነሱ ጋዜጠኞችና ታዛቢዎች ሃሳብ ተገቢ መሆኑንም ገልጿል፡፡
አሸባሪው ህወሃት ከምስረታው ጀምሮ በዜጎች ደምና ስቃይ በመነገድ የሚታወቅ ድርጅት ሲሆን፤ በ1977 ዓ.ም በትግራይ በተከሰተው ረሃብ የፈጸመው ዘግናኝ ድርጊት ደግሞ ለዚህ ጥሩ ማሳያ ነው፡፡
ቡድኑ ከደርግ መንግስት ጋር የትጥቅ ትግል እያደረገ በነበረበት በ1977 ዓ.ም በትግራይ እጅግ አስከፊ ረሃብ መከሰቱ ይታወሳል፡፡
ወትሮውንም ለህዝብ ደንታ የሌለው ይህ ቡድን በረሃብ የሚረግፉ ዜጎችን ሰቆቃ እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ከመላው ዓለም የተራድኦ ድርጅቶች፣ ግለሰቦችና ተቋማት የሚቀርበውን እርዳታ ለመሳሪያ ግዥ ተጠቀመበት፡፡
በአንድ ወቅት የእንግሊዙ ታወቂ የቴሌቭዥን ጣቢያ (ቢቢሲ) ባሰራጨው መርማሪ ዘገባ ህወሃት በወቅቱ በእርዳታ ከሚቀርበው እህል ውስጥ 5 በመቶውን ብቻ ለህብረተሰቡ በማድረስ ቀሪውን ለመሳሪያ ግዥ ይጠቀምበት እንደነበር ከቡድኑ መስራቾች መካከል ዶክተር አረጋዊ በርሄን ጠቅሶ መዘገቡ አይዘነጋም፡፡
በዚህም በትግራይ በርካታ ዜጎች በረሃብና ቸነፈር ምክንያት ለሞት ተዳርገዋል፡፡
“ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ” እንዲሉ አሸባሪው ህወሃት አሁንም ወደ ትግራይ የሚገባውን እርዳታ ለጦርነት ዓላማ እየተጠቀመበት መሆኑን የሚያነሱ ዓለም አቀፍ ጋዜጠኞችና ታዛቢዎች ተበራክተዋል፡፡
ኒውዝላንዳዊው ጋዜጠኛ አልስቴር ቶምሰን ከኢዜአ ጋር በነበረው ቆይታ አሸባሪው ህወሃት ሰብዓዊ ድጋፎችን ለጦርነት የማዋል ልምድ ያለው ድርጅት መሆኑን አንስቷል፡፡
የሽብር ቡድኑ በ19 80ዎቹ በሰሜን ኢትዮጵያ ተከስቶ የነበረውን ረሃብ ተከትሎ ከዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅቶች ይቀርብ የነበረውን ሰብዓዊ ድጋፍ ለጦር መሳሪያ ግዥ እንዳዋለው አስታውሷል።
ቡድኑ አሁንም ተመሳሳይ ድርጊት እንደሚፈጽም ነው ጋዜጠኛው የሚያብራራው፡፡
የሽብር ቡድኑ እርዳታ ጭነው ወደ ትግራይ ክልል የገቡ ተሽከርካሪዎችን በማገት ለጦርነትና በወረራ ይዟቸው በነበሩ አካባቢዎች ንብረት ለመዝረፍ መጠቀሙንም ነው የገለጸው፡፡
ቡድኑ የእርዳታ መጋዝኖችን በመዝረፍ ጭምር የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሃብትን ለጦርነት ማዋሉ ግልጽ ነው ሲል አብራርቷል፡፡
“የመንግስታቱ ድርጅት ይህን የቡድኑን ህገ-ወጥ አካሄድ በግልጽ ሲያወግዝ አይታይም፤ ይህም ተቀባይነት የሌለውና የዓለም አቀፍ መርሆችን የጣሰ አካሄድ ነው” ብሏል፡፡
ከዚህ አኳያ ዓለም አቀፍ የእርዳታ ድርጅቶች ጉዳዩን በሚመለከት ጥያቄ ላላቸው አካላት ምላሽ ሊሰጡ እንደሚገባም ነው የተናገረው፡፡
ቡድኑ በተለይ በአፋር ክልል የእርዳታ መስመሮች ላይ ወረራ በመፈጸም ሰብዓዊ ድጋፍ ወደ ትግራይ እንዳይገባ ሲፈጽም የነበረውን ህገ-ወጥ ተግባር የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ሊገነዘብ እንደሚገባም ተናግሯል፡፡
በመሆኑም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ወደ ትግራይ ክልል የሚላከውን ሰብዓዊ እርዳታ ለምን ዓላማ እየዋለ መሆኑን በአግባቡ ማጣራት እንደሚጠበቅበት ተናግሯል፡፡
በተያያዘ የዓለም የጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም ከድርጅቱ መርህ ባፈነገጠ መልኩ በሰሜን ኢትዮጵያ ስላለው ሁኔታ የተሳሳተ መረጃ እያሰራጩ መሆኑን ጋዜጠኛው ተናግሯል፡፡
በመሆኑም የመንግስታቱ ድርጅት የዓለም የጤና ድርጅትን ጨምሮ በስሩ ያሉ ተቋማትን አሰራር መለስ ብሎ ሊመረምር ይገባል ነው ያለው፡፡
የዓለም የጤና ድርጅትን ዋና ዳይሬክተር እያከናወነ ያለው ተግባር ትክክል አለመሆኑ በግልጽ ሊነገረው እንደሚገባም ነው ያነሳው፡
ENA
- Ethiopia Working To Secure New Development Bank MembershipThe Ministry of Foreign Affairs disclosed that Ethiopia is working hard to become member of BRICS’ New Development Bank. In a media briefing regarding the country’s diplomatic activities over the week, Spokesperson of the Ministry Nebiyu Tedla, indicated that Ethiopian delegation led by State Minister of Foreign Affairs Ambassador Mesganu Arga participated in the consultation… Read more: Ethiopia Working To Secure New Development Bank Membership
- National Dialogue, Transitional Justice And Rehabilitation Process Pillars of Lasting Peace, Prosperity: CouncilThe Ethiopian National Security Council has issued a statement on latest developments in the country. In its statement, the Council underscored the need to mend the deep-seated national fractures through an inclusive approach. According to the council, three problem-solving mechanisms are put in place so as to address the existing and new political challenges resulted… Read more: National Dialogue, Transitional Justice And Rehabilitation Process Pillars of Lasting Peace, Prosperity: Council
- Somaliland offended by G7 referring the Republic of Somaliland as “Somaliland Region of Somalia” The Republic of Somaliland, is a sovereign state with its own laws and constitution, reaffirmed by the people of Somaliland in a democratic constitutional referendum. The Government of the Republic of Somaliland’s Statement Regarding the G7 Communique First and foremost, the Government and the people of the Republic of Somaliland are deeply offended by the… Read more: Somaliland offended by G7 referring the Republic of Somaliland as “Somaliland Region of Somalia”