Site icon ETHIO12.COM

“ኡሁሩ ኬንያታ የትግራይ አማጺ ቡድን ደጋፊ መሆናቸውን ይፋ አደረጉ”

ፎቶ - የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በግጭት ላይ ያሉ ሁሉም አካላት በአፋጣኝ ወደ ድርድር እንዲመጡ በጠየቁበት ወቅት ይህንኑ ለኬንያው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ማማከራቸው ተጠቅሶ በተዘገበበት ወቅት የተሰራጭ ምስል ነው

ቅዳሜ ለሚደረገው የሰላም ንግግር በፕሮግራም መደራረብ ምክንያት እንደማይሳተፉ ያስታወቁት ኡሁሩ ኬንያታ የትግራይ አማሺ ቡድን ደጋፊ መሆናቸውን በይፋ ማስታወቃቸውን ለአፍሪካ ህብረት ጻፉት የተባለውን ደብዳቤ ያዩ አስታወቁ። ደብዳቤያቸው በማጠቃለያው ላይ የቡድኑ መሪ ዶክተር ደብረጽዮን ለአፍሪካ ህብረት በርዕስ ለኡሁሩ በግልባጭ ከላኩት ደብዳቤ ጋር የቅጂ ያህል ተመሳሳይነት እንዳለውም ተመልክቷል።


መንግስት አማጺ ሲል የሚጠራው ቡድን መሪ ዶክተር በደብረ ጽዮን ገብረሚካኤል ተፈርሞ በርዕስ ለአፍሪካ ለኅብረት ሊቀ መንበር የተላከው ደብዳቤ የሰላም ድርድር ግብዣ መቀበላቸውን አረጋግጦ፣ ድርድሩ ጅምሩ የተሳካ እንዲሆን ሲል አስቀድሞ አንዳንድ ማብራሪያዎችን እንዲሰጡት ጠይቋል። የሰላም ወይይቱ ተሳታፊዎች፣ ታዛቢዎችና ዋስትና ሰጪዎች አካላት ተጋብዘው እንደሆነም እንዲነገረው አመክቷል። የዓለም አቀፉ ኅብረተሰብ ስለሚኖረው ሚናም ኅብረቱ ዝርዝር እንዲያቀርብ አስታውሷል። ከተደራዳሪዎች ደህንነትና ሎጂስቲክ በተጨማሪ “ጦርነቱን ማቆም የኅብረቱ ዋና አጀንዳ አካል መሆኑን ማወቅ ለሰላም ሂደቱ ጠቃሚ ይሆናል” ሲል አክሏል። በተዘዋዋሪ መንግስት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የተቀበለውን የሰላም ወይይት በተኩስ ማቆም ስምምነት እንዲታሰርለት መጠየቁ ድርጅቱ አሁን ካለበት ወቅታዊ ቁመናው የሜመነጭ እንደሆነ ለክርከር ባማይቀርበበት ደረጃ ይታመናል። ኡሁሩም ይህንኑ ቃል በቃል ደግመው ተኩስ አቁም ስምምነት አስገዳጅ እንዲሁን ተስፋ እንደሚያደርጉ አመልክተዋል።


ኡሁሩ ኬንያታ በሰላም ንግግሩ ውስጥ እንደማይሳተፉ፣ ይህም የሆነው በፕሮግራም መደራረብ እንደሆነ፣ ወደፊት የሚሳተፉ ከሆነ ደግሞ ሊሆን ይገባል ያሉትን ቅድመ ሁኔታ ትህነግን ወክለው በድብዳቤያቸው ላይ አስፍረዋል። ደብዳቤውን ያዩ እንዳሉት ኡሁሩ አማጺው ቡድን ከጻፈው ደብዳቤ ጋር በተመሳሳይ “ማብራሪያ ይሰጠኝ” በሚል ሽፋን ያስቀመጡት ቅድመ ሁኔታ አስቸኳይ ተኩስ አቁም፣ የጥላቻ ንግግር ( ፓርላማው ትህነግን አሸባሪ ብሎ መፈረጁ ይታወሳል) አጀንዳ አስቀድሞ እንዲቀረጽ፣ የንግግሩ አወቃቀርና አፈጻጸምና የመሳሰሉትን ጉዳዮች ነው።

ኡሁሩ አፍሪካ ህብረት በኦክቶበር አንድ የጻፈው ደብዳቤ በደረሳቸው በሁዋላ በኦክቶበር ሰባት በመለሱት ምላሽ “የፕሮግራም መደራረብ አለብኝ” ማለታቸውና ቅዳሜ እንዲደረግ በተያዘው ፕሮግራም ላይ መገኘት እንደማይችሉ ማስታወቃቸው ሴራ እንዳለው ያመለከቱ ” ኡሁሩ ምን አልባትም በደም ጉዳይ አለቆቻቸው ተብትበው ስለያዟቸው አድርጉ የተባሉትን ከማድረግ ወደሁዋላ አይሉም” ሲሉ ወደ 2007 ምርጫ ያመልክታሉ።

ለበርካታ ንጹሃን ሞት፣ መፈናቀል፣ በመላው አገሪቱ በጥምረት እየተከናወነ ያለውን መንታ ጦርነት እልባት እንደሚሰጥ ሰፊ ግምት የተሰጠውን ንግግር ከሰባት ቀን በሁዋላ ” አልችልም” በሚል ያፈረሱት ኡሁሩ አፈትልኮ የወጣውን ጄነራል ጻድቃን ገብረትንሳኤ ከሪፖብሊካን ፓርቲ ቲንክ ታንክ Heritage Foundation ጋር ያደረገው ቃለመጠይቅ ድርድርን አስመልክቶ ሲጨመቅ ተመሳሳይ እንደሆነ

“ለዚህም ነው የቱንም ያህል ጠቅላላ ብሄራዊ ምርት ቢኖራት ኬንያ የአፍሪካውያን መሳቂያ ከመሆን ያልዳነችው። ባራክ! ኬንያ ለከፈላት ሁሉ እግሯን የምትከፍት የአፍሪካ ሸርሙጣ ነች ” ስትል ነበር ምሬቷን ለወንድሟ የገለፀችው። ( Dreams from My Father, Barack Obama, page 312-314)
ዋናው ሚስጥር ይሄ ነው! ኬንያ ለከፈላት የምታገለግል ሴተኛ አዳሪ ነች! በሚከፈላት ዶላር ልክ አቤት ወዴት ብላ የምታጎበድድ የፈረንጅ ተላላኪ ስለሆነች ነው በቀድሞ ፕሬዝዳንቷ ኡህሩ ኬንያታ አማካኝነት የኢትዮጵያ መንግስትና የወያኔ አደራዳሪ እንድትሆን በእነአሜሪካ የተመረጠችው።

ሙሉውን እዚህ ላይ ያንብቡ

በመንግስትና በትግራይ አማጺ ኃይሎች መካከል ንግግር ይጀመራል ከተባለበት አንድ ቀን በፊት በሎጂስቲክ ምክንያት ስብሰባው መሰረዙ ተገልጿል። ይህንኑ ተከትሎ “ተስፋ አደርጋለሁ” በሚል ኡሁሩ ያጻፉት ቅድመ ሁኔታ ያካተተ ደብዳቤ ” ትህነግ ፎክሮ በጉልበት ሲበለጥና አጣብቂኝ ውስጥ ሲገባ የተወው ቅድመ ሁኔታ በኡሁሩ አማካይነት ተለሳልሶ መቅረቡና ለማሸማገል ቅድመ ሁኔታቸው መሆኑ በስልታን ጊዜያቸው ኢትዮጵያ ላይ የፈጸሙትን ክህደት አመልካች ነው” ሲሉ የዘለፏቸው ጥቂት አይደሉም።

በሁለተኛው ወረራ ወቅት በጸጥታው ምክር ቤት፣ እንዲሁም በናይሮቢ በሚጠነሰስ ጥንስስ ኡሁሩ ሰፊ ሚና እንደነበራቸው፣ የኢትዮጵያ መንግስት ይብቃው አይነት ንግግር ማሰማታቸውን ያስታወሱ ኡሁሩ አለቆቻቸው አድርጉ የሚሏቸውን ከማድረግ ወደሁዋላ እንደማይሉ የሚጠቁሙት በማስረጃም ጭምር ነው።

በ2007 ምርጫ ድምጽ አጭበብረው የነበሩት ኡሁሩ የሳቸውን ማጭበርበር ተለትሎ በተነሳ አመጽ ከአንድ ሺህ በላይ ንጹሃን መገደላቸው፣ በሃይል እንዲሰደዱ፣ እንዲደፈሩና ስቃይ እንዲሰድርስባቸው በተደረጉ ዜጎች የመብት ጥሰት እነ ባራክ ኦባማ ወደ ዓለም ዓቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት እንደሚወስዷቸው በገሃድ ሲናገሩ ነበር። ይኸው በአገራቸው ፍርድ ቤት ተደፋፍኖ የቆየው የደም ወንጀል ኡሁሩ ሳይጠሩ አቤት፣ ሳይላኩ ወዴት ባይ ከመሆን የዘለለ እድል እንደማይሰጣቸው የሚገልጹ ” እቃ” ይሏቸዋል።

” በዚሁ የመላላክና የአሽከርነት መመሳሰል ትህነግ ኡሁሩ በሸምጋይነት ካለገቡ” ሲል የወተወተበት ምክንያት ለአፍሪካ ህብረት በሳፉት ደብዳቤ በገሃድ መረጋገጡን ያወሱ ” መንግስት ዙሩን ማክረር፣ ደጀኑ ጡንቻውን ማፈርተም፣ ህዝብ አንድነቱን ማደርጀት፣ እንደ አገር ትግራይንና የትግራይን ንጹሃን ነጻ ለማውጣት ተናቦ መስራት ግድ ነው” ብለዋል። “ኡሁሩ ግን የተኩስ አቁም አስገዳጅ ሁኔታ ሊኖር እንደሚገባ አለሳልሰው በማቅርብ ለትህነግ ስልታዊ ፋታ ጠይቀዋል።በዚህም የትግራይ አማጺ ቡድን አባልና ደጋፊ መሆናቸውን በይፋ አስታውቀዋል” ሲሉ ተናገረዋል።

Exit mobile version