Site icon ETHIO12.COM

መከላከያ በክህደት የተጨፈጨፈበት ቀን በኢትዮጵያዊያን ልብ ውስጥ ታትሟል – ዜጎች ሁሉ ነገ ሰግደው ቀኑን ያስባሉ

ጥቅምት ፪፬ ከሃጂ የት ህነግ አመራሮችና ጀሌዎቻቸው የኢትዮጵያን ውድ ልጆች አረዱ። አሳረዱ። በመኪና ፈጯቸው። አህቶቻችንን ደፈሩ፣ አካላቸውን ቆራረጡ። በጎዳና አሰልፈው አህያ እያሉ ተዛበቱባቸው። ለሃያ ሁለት ዓመታት በቀበሮ ጉድጏድ የታተመን ፍቅር ከሃጂዎች ሰቀሉት። ሰቅለው አላበቁም ቅ ጽበታዊና መብረቃዊ፣ በደቂቃዎች የተከወነ ሲሉ በክህደታቸው ተመጻደቁ። አውካኩ። ርችት ተኮሱ። አስከሪአናቸውን ለ አውሬ በትነው ጀግና ሆነው ተኮፈሱ። ኢትዮጵያ አለቀሰች። ሆድ ባሳት። ራሳቸው በትዕቢት ምስክርነት ስለሰጡ ማስተባበል አልተቻለምና ሕዝብ አመረር።
ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር አብረው ኢትዮጵያን በሃዘኗ ላይ ዓይኗን ለማፍሰስ በየስርቻው አሴሩ። በወጉ ሃዘኗን ያልተቀመጠችው ኢትዮጵያ ከሃጂና ባንዳን ማራገፍ በለመደ ክንዷ አበረችና ልጆቿን ያረዱትን የባንዳዎች ቁንጮ አቀለጠች። ክህደቱ በተፈጸመ ልክ በሁለት ዓመቱ ኢትዮጵያ ባንድ አጇ የስንዴ ዛላ፣ በሌላ አጇ የህጻናት ማበልጸጊያ ማሳ፣ በተቀረው ኢትዮጵያ የምጸራበትን የሳይንስ ማዕከል ገንብታ ከሃጂዎችን ቀበረች። ባንዳም፣ የባንዳ ባንዳም እርም አወጣ። የኢትዮጵያ ክንድ ብቻ ሳይሆን ዲፕሎማሲና አይበገሬነት በሕዝቧ ኮስታራነት አሸናፊ ሆነ። በስሙ የሚማልበት የትግራይ ሕዝብም መከላከያ በታረደበት ቀን ነጻ ሆነ። ድርብና ታላቅ ታሪካዊ ትርጉም ያለው ይህ የክቡር ልጆቻችን መታሰቢያ በመላው ኢትዮጵያ ትግራይን ጨምሮ በጸጥታ፣ በመንቀጥቀጥ፣ በክብርና በፍቅር ውዶቻችን፣ የመኖራችን ሚስጢሮች አንረሳች ሁም ተብሎ ይታሰባል። ልክ ከጠዋቱ አራት ሰዓት

ጥቅምት ፪፬ ከሃጂ የት ህነግ አመራሮችና ጀሌዎቻቸው የኢትዮጵያን ውድ ልጆች አረዱ። አሳረዱ። በመኪና ፈጯቸው። አህቶቻችንን ደፈሩ፣ አካላቸውን ቆራረጡ። በጎዳና አሰልፈው አህያ እያሉ ተዛበቱባቸው። ለሃያ ሁለት ዓመታት በቀበሮ ጉድጏድ የታተመን ፍቅር ከሃጂዎች ሰቀሉት። ሰቅለው አላበቁም ቅ ጽበታዊና መብረቃዊ፣ በደቂቃዎች የተከወነ ሲሉ በክህደታቸው ተመጻደቁ። አውካኩ። ርችት ተኮሱ። አስከሪአናቸውን ለ አውሬ በትነው ጀግና ሆነው ተኮፈሱ። ኢትዮጵያ አለቀሰች። ሆድ ባሳት። ራሳቸው በትዕቢት ምስክርነት ስለሰጡ ማስተባበል አልተቻለምና ሕዝብ አመረር።
ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር አብረው ኢትዮጵያን በሃዘኗ ላይ ዓይኗን ለማፍሰስ በየስርቻው አሴሩ። በወጉ ሃዘኗን ያልተቀመጠችው ኢትዮጵያ ከሃጂና ባንዳን ማራገፍ በለመደ ክንዷ አበረችና ልጆቿን ያረዱትን የባንዳዎች ቁንጮ አቀለጠች። ክህደቱ በተፈጸመ ልክ በሁለት ዓመቱ ኢትዮጵያ ባንድ አጇ የስንዴ ዛላ፣ በሌላ አጇ የህጻናት ማበልጸጊያ ማሳ፣ በተቀረው ኢትዮጵያ የምጸራበትን የሳይንስ ማዕከል ገንብታ ከሃጂዎችን ቀበረች። ባንዳም፣ የባንዳ ባንዳም እርም አወጣ። የኢትዮጵያ ክንድ ብቻ ሳይሆን ዲፕሎማሲና አይበገሬነት በሕዝቧ ኮስታራነት አሸናፊ ሆነ። በስሙ የሚማልበት የትግራይ ሕዝብም መከላከያ በታረደበት ቀን ነጻ ሆነ። ድርብና ታላቅ ታሪካዊ ትርጉም ያለው ይህ የክቡር ልጆቻችን መታሰቢያ በመላው ኢትዮጵያ ትግራይን ጨምሮ በጸጥታ፣ በመንቀጥቀጥ፣ በክብርና በፍቅር ውዶቻችን፣ የመኖራችን ሚስጢሮች አንረሳች ሁም ተብሎ ይታሰባል። ልክ ከጠዋቱ አራት ሰዓት

አሸባሪው የህወሓት ቡድን በሰሜን ዕዝ ላይ ክህደት የፈፀመበት ጥቅምት 24 ቀን “መቼም አንረሳውም” በሚል መሪ ቃል ታስቦ ይውላል፡፡

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የሰሜን ዕዝ በአሸባሪው የህወሓት ቡድን በጥቅምት ሃያ አራት ቀን 2013 ዓ.ም ጥቃት ያደረሰበትን ሁለተኛ ዓመት መታሰቢያ ዕለትን በማስመልከት መገለጫ ሠጥቷል።

በመግለጫው የጥቅምት 24 መታሰብ ዋና ዓላማ ጀግናው የመከላከያ ሰራዊታችን ለከፈለው እና እየከፈለው ላለው መስዋዕትነት ዕውቅናና ክብር ለመስጠት ነው ብሏል።

የፊታችን ጥቅምት 24 ከማለዳው 4 ሰዓት ለአንድ ደቂቃ ያክል ተማሪዎች፣ አሽከርካሪዎችና የፀጥታ ኃይል አባላትን ጨምሮ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ቆሞ ለሀገር መከላከያ ሰራዊት ያለውን ክብርና አጋርነት ያሳያልም ተብሏል።

የሀገር መከላከያ ሰራዊትን ተጋድሎ ለማሰብ በተዘጋጁ መርሐ-ግብሮችም ሁሉም ኢትዮጵያዊ በንቃት እንዲሳተፍ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ጥሪውን አቅርቧል።

ጥቅምት 24 ሠራዊታችን ጓዶቹን ያጣበት ቀን በመሆኑ በተለያዩ የሠራዊቱ ክፍሎችም ዕለቱ ታስቦ ይውላል። ዘላለማዊ ክብር ለሰሜን ዕዝ ሰማዕታት

Exit mobile version