ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት በይፋ እንደምትንቀሳቀስ ባሳወቀች ማግስት የአውዳል ግዛት ንቅናቄ በይፋ ጥሪ አቅርቧል። ሶማሌ ዳይጀስት እንደዘገበው ንቅናቄው ሁሉንም ወገን አሸናፊ የሚያደርግ የመግባቢያ ስምምነት እንዲደረግም ፍላጎት እንዳለው አስታውቋል። ከመንግስት ወገን ለጊዜው የተባለ ነገር የለም።
በሶማሊላንዷ አውዳል ግዛት የሚገኘው The Awdal State Movement – ASM ኢትዮጵያ በቀይ ባሕሯ የዘይላ ወደብ እንድትጠቀም ፈቃዱን አሳውቋል። የ ASM ንቅናቄ ባለፈው አርብ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫው በተለይም የዘይላ ወደብን ከግምት አስገብቶ በመጥቀስ ነው ለኢትዮጵያ የወደብ አማራጭ መሆኗን እንቀበላለን ያለው።
በዚህ መግለጫ ‘ጋዳቡርሲ’ የተሰኘው የአካባቢው ማህበረሰብ በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ታሪካዊ እና ወቅታዊ ፋይዳ በመገንዘብ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ጂኦግራፊያዊ እና ታሪካዊ ትብብር እንደሚያስፈልግ አፅንዖት ሰጥቷል። በበተጨማሪም ታሪካዊው የዘይላ ወደብ የኢትዮጵያ ሱማሌዎችን በመጥቀስ የኢትዮጵያ ህዝብ መጠቀማቸውን እንደሚደግፍ የገለፀ ሲሆን፣ ለስኬቱም ሁሉንም ወገን አሸናፊ በሚያደርግ የመግባቢያ ስምምነት ይደረግ ዘንድ በደስታ የምንቀበለው ነው ብሏል።
የአውዳል መንግስት ንቅናቄ ASM በሰሜን ምዕራብ ሶማሊላንድ የምትገኘውን አውላድ ግዛት እየመራ የሚገኝ ሲሆን፣ በቅርቡ(ከሳምንታት በፊት) ይፋ ባደረገውና ወደ ሶማሊያ/ሞቃዲሾ የመዋሃድ ውሳኔውን ለመተግበር ከራስ-ገዝ ሶማሊላንድ የተነጠለ አቋሙን እወቁልኝ ብሏል። ይህን ተከትሎም የሶማሊላንድ ጦር ከአውላድ ግዛት ለቅቆ እንዲወጣ ሆኗል። በምትኩም የአውላድ ንቅናቄ ኃይሎች የፀጥታ ኃላፊነቱን ተረክበዋል።
የ ASM ንቅናቄ ወደ ሶማሊያ በሚያደርገው ውህደት ውስጥ ከውጭ ዲያስፖራዎችም ም ሆነ ከሀገረ ሶማሊያ ዜጎችና ልሂቃን ሰፊ ድጋፍ እያገኘ ሲሆን፣ ከዚህ ሂደት በተያያዘ የዘይላ ወደብን ኢትዮጵያ ትጠቀምበት ዘንድ ያቀረበው የግብዣ መግለጫው “ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ተገቢውን ምክክር ያድርግ” ከሚለው በስተቀር ይህ ነው የሚባል ይፋዊ ተቃውሞ አልገጠመውም።
የአውላድ ንቅናቄ ተፈላጊነት አጥቶ በሚገኘው የዘይላ ወደብ ኢትዮጵያ ትጠቀምበት ዘንድ አመክንዮ ናቸው በማለት በይፋ የጠቀሳቸው የኢኮኖሚ፣ የታሪክና የሕዝብ ትስስር ጉዳዮች ቅቡላዊ መሆናቸው ግልፅ ቢሆንም፣ ከአዲስ አበባ ጋር እንዲፈረም ያቀረበው ምክረ ሐሳቡ፣ ከሐርጌሳ ሶማሊላንድ የሀገርነት እውቅና ጉጉት ጋር የሚቃረን እሳቤ ይኖረው ይሆን? የሚለውን ጊዜ የሚመልሰው ጥያቄ ነው የሚሆነው።
ኢትዮጵያ የዘይላ ወደብን ለማስመለስ በርካታ ጥረቶች ማድረጓ የሚታቅ ሲሆን በተለይም በቀዳሚ ኃይለ ስላሴ በኩል አስርት አመታትን የተሻገረው ጥረት በቅኚ ገዢዎቹ እንግሊዝ፣ ጣልያንና ፈረንሳይ የጥቅም ስሌት ሳቢያ ሳይሰምር ቀርቷል።
ሶማሊላንድ ውስጥ የእንግሊዝ ጥቅም ስር የሰደደ ሲሆን ዋሽንግተንም በተመሳሳይ ትብብር ላይ ነው የምትገኘው። እንግሊዝና አሜሪካ ለሶማሊላንድ እውቅና ለመስጠት በተለይም ከአመት ወዲህ ሰፊ ስራ የጀመሩ ሲሆን ሀርጌሳም ይህን ለማሳካት ከመቸውም በላይ ጥረት በማድረግ ላይ ነው የምትገኘው። በአንፃሩ ከሶማሊያ ተነጥለው የቆዩ ግዛቶች (የአውላድ ግዛትን ጨምሮ) ወደ ቀድሞ ‘የግዛት አካልነታችን’ እንመለስ የሚሉ ፍላጎቶች እየበረቱ መምጣታቸው፣ በምዕራባዊያን ከሚደገፈው የሐርጌሳ መንግስት የእውቅና ፍላጎት ጋር መቃረኑ ተጠባቂ ተግዳሮት ይሆናል።
ኢትዮጵያ የወደብ ባለቤት ትሆን ዘንድ መሰል ቀና ፍላጎቶች መታየት መጃራቸው በራሱ ትልቅ ፋይዳ ያለው ነው። በተለይም ኢትዮጵያ አፍነው የቆዩ ባለ ወደብ ጎረቤቶቻችን ነባሩን ‘ወደብ ቋጣሪ’ አቋማቸውን እንደገና ይፈትሹ ዘንድ የሚያስገድድ ነው።
በየዓባይ:ልጅ
- ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋገጡ፤ በትግራይ አስተዳደር ስም ማስተባበያም አውጥተዋልበሱዳን ለአንድ ዓመት የዘለቀው የእርስ በእርስ እልቂት ብዙ ተዋንያኖች አሉበት። ከአርቡ ዓለም፣ ከአውሮፓ፣ ከአፍሪቃ፣ ሩሲያና አሜሪካንን ጨምሮ የተለያዩ አካላት የሚዳክሩበት በዚህ ጦርነት የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ… Read more: ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋገጡ፤ በትግራይ አስተዳደር ስም ማስተባበያም አውጥተዋል
- Are Tigray mercenaries fighting in conflict-ravaged Sudan?Mercenaries from Ethiopia’s Tigray People’s Liberation Front are fighting alongside Sudanese army regulars against fighters of the Rapid Support Forces (RSF), the paramilitary group is claiming.… Read more: Are Tigray mercenaries fighting in conflict-ravaged Sudan?
- Sudan’s RSF Accuse Tigray People’s Liberation Front of Backing SAFSudanese warring party Rapid Support Forces has officially accused the Tigray People’s Liberation Front Fighters of fighting in Sudan in support of the Sudanese Armed Forces… Read more: Sudan’s RSF Accuse Tigray People’s Liberation Front of Backing SAF
- የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ“ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ” እያሉ በስሟ ሲምሉ የነበሩ ብዙዎች ነበሩ፤ ከልባቸው ለቃላቸው ታምነው ልጅ የሆኗት ግን ጥቂቶች ብቻ ናቸው። አንዳንዶች በስሟ የሚገዘቱት እንጀራዋን ለመብላት እንጂ መከራዋን ለመካፈል አይደለም፤… Read more: የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ
- አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ“ወገኖቼ እንማርና እናስተምር፣ ወንጀልን እንጸየፈው፣ እንጥላው፣ ወንጀልን ተጸይፈን ወንጌልን እንውደደው፣ በወንጌል እንኑር፣ ወንጌል ሕጓም ስርዓቷም ያማረች ናት፤ ወንጌላዊ መኾን መልካም ነው፣ ወንጀለኛ መኾን ግን ሐጥያት ነው… Read more: አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ