የመከላከያ ሚኒስቴር ኢንዶክትርኔሽን ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጀኔራል መሀመድ ተሰማ ዛሬ ይፋ እንዳደረጉት አስራ ስምንት ከፍተኛ መኮንኖች በቁጥጥር ስር ውለዋል። እነዚህ ከፍተኛ መኮንኖች የተያዙት በፍተሻና በመከላከያ ሠራዊትና የፌዴራል ጸጥታ ሃይሎች የጋራ አሰሳና ፍተሻ ነው።
ከጁንታው የጥፋት ቡድን ጋር በማወቅም ይሁን ባለማወቅ የተሰለፉ ሃይሎች በሰላማዊ መንገድ እጃቸውን ለመንግስት እንዲሰጡም በድጋሚ ጥሪ ቀርቧል። የመከላከያ ኢንዶክትርኔሽን ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጀኔራል መሀመድ ተሰማ ለኢዜአ አንደገለጹት 18ቱ ከፍተኛ መኮንኖች በቁጥጥር ስር የዋሉት የመከላከያ ሰራዊትና የፌደራል ጸጥታ ተቋማት በቅንጅት ባካሄዱት አሰሳና ፍተሻ ነው።
በቀጥጥር ስር ከዋሉት መኮንኖች መካከል ዘጠኙ የሙሉ ኮሎኔል ማዕረግ፤ ሰባቱ የሌተናል ኮሎኔል ማዕረግ ያላቸውና ሁለቱ ደግሞ የፖሊስ ኮማንደሮች መሆናቸውን ገልጸዋል። ሜጀር ጄኔራል መሃመድ፤ ወንጀለኞችን የማደኑ ተግባር ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል።
ከጁንታው የጥፋት ቡድን ጋር በማወቅም ይሁን ባለማወቅ የተሰለፉ ሃይሎች በሰላማዊ መንገድ እጃቸውን ለመንግስት እንዲሰጡም ሜጀር ጄኔራሉ በድጋሜ ጥሪ አቅርበዋል። ህዝቡም ለፀጥታ ሃይሉ እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ መቀጠሉንም ተናግረዋል።
በቅርቡ ከጁንታው የጥፋት ቡድን ጋር ተሰልፈው ከነበሩት ከፍተኛ መኮንኖች መካከል ሜጀር ጄኔራል መሀመድ እሻን ጨምሮ ሌሎች የጁንታው ከፍተኛ የጦር መኮንኖች እጃቸውን መስጠታቸው ይታወሳል።
- የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ
by topzena1
“ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ” እያሉ በስሟ ሲምሉ የነበሩ ብዙዎች ነበሩ፤ ከልባቸው ለቃላቸው ታምነው ልጅ የሆኗት ግን ጥቂቶች ብቻ…
Read more: የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ
- አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ
by topzena1
“ወገኖቼ እንማርና እናስተምር፣ ወንጀልን እንጸየፈው፣ እንጥላው፣ ወንጀልን ተጸይፈን ወንጌልን እንውደደው፣ በወንጌል እንኑር፣ ወንጌል ሕጓም ስርዓቷም ያማረች…
Read more: አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ
- ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናው
by topzena1
ቤት የተባለች አንዲት ሴት እንዲህ ብላለች፦ “ደም ማነስ የያዘኝ በአሥራዎቹ ዕድሜ ሳለሁ ነው። ቶሎ ይደክመኝ፣ አጥንቶቼን…
Read more: ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናው
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
by topzena1
ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ…
Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?