ለክቡር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራ የምስጋና እና እውቅና ፕሮግራም እንደሚካሄድ የኦሮሚያ ባህል እና ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ።የቢሮው ኃላፊ አቶ ከበደ ዴሲሳ ዛሬ በሰጡት መግለጫ የእውቅና እና የምስጋና ፕሮግራሙ ጥር 30 ቀን 2013 ዓ.ም ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ፣አድናቂዎቹ እና የአርቲስቱ ወዳጆች በተገኙበት ይካሄዳል፡፡
መርሃ -ግብሩም አርቲስቱ ከ60 ዓመታት በላይ ለኦሮሞ ኪነ-ጥበብ እድገት ላበረከተው ጉልህ አስተዋጽኦ እውቅና ለመስጠት መዘጋጀቱን ነው የገለጹት።አርቲስቱ ለኢትዮጵያ ህዝቦች አብሮነትና ማህበራዊ ትስስር ከፍ ያለ አስተዋጽኦ ማበርከቱንም ጨምረው ተናግረዋል።በሙዚቃዎቹ ዘመን ተሻጋሪ መልዕክቶችን በማስተላለፍ መልካም ትውልድ እንዲቀረጽ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል ነው ያሉት።
በወቅታዊ ክስተቶች ሳይሸነፍ በከፍተኛ ጽናትና ብቃት ለረጅም ዓመታት በኪነ ጥበቡ ውስጥ ያሳለፈ መሆኑ ደግሞ አሁን ላለው ትውልድ ታላቅ ተምሳሌት እንደሚያደርገውም አውስተዋል።መርሃ ግብሩ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ፣አድናቂዎቹ እና የአርቲስቱ ወዳጆች በተገኙበት እንደሚካሄድም ተገልጿል።ጥር 30 ቀን 2013 ዓ.ም በሚካሄደው መርሃ ግብርም የአርቲስቱ የሕይወት ታሪክ እና ሥራዎች ላይ የተፃፈ መጽሐፍ እንደሚመረቅም ነው የተናገሩት።
ክቡር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራ በ1954 ዓ.ም የተመሰረተውን የመጀመሪያው የኦሮሚኛ ቋንቋ የኪነት-ቡድን “አፍረን ቀሎ”ን በመቀላቀል ነበር የሙዚቃ ስራውን የጀመረው።አርቲስቱ ከኦሮሚኛ በተጨማሪ፣በሱማሊኛ፣በአፋርኛ፡በሐረሪ፣በአማርኛና በሱዳን ቋንቋዎች በርካታ ዘፈኖችን መጫወት ችሏል።
( ኢዜአ)
- ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናው
by topzena1
ቤት የተባለች አንዲት ሴት እንዲህ ብላለች፦ “ደም ማነስ የያዘኝ በአሥራዎቹ ዕድሜ ሳለሁ ነው። ቶሎ ይደክመኝ፣ አጥንቶቼን ይቆረጥመኝ፣ እንዲሁም ትኩረቴ…
Read more: ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናው
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
by topzena1
ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ ወገኖች አስታውቀዋል። ጎን…
Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት
by topzena1
ዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ። ለውጭ አገር ሚዲያዎች…
Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት
- የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡም
by topzena1
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የትራንስፖርት ስምሪትና የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር ሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ 11 ግለሰቦች በስር ፍ/ቤት የተሰጠውን ዋስትና አፀና።…
Read more: የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡም