ለዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር 6 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኝ ለመትከል ዕቅድ መያዙንna ለዚህም ተግባራዊነት ከሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊየን በላይ ችግኝ መዘጋጀቱን ተገለጸ። 1 ነጥብ 2 ሚሊየን ሄክታር መሬት ለተከላ ተዘጋጅቷል።
ለዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በቂ ቅድመ ዝግጅት መተናቀቁን ያመልከቱት የግብርና ሚኒስትሩ ዶ/ር ግርማ አመንቴ ባለፈው ዓመት የተተከለው ችግኝ ዘጠና በመቶ የመጽደቅ ደረጃ መድረሱን አመልክተዋል።
በኢትዮጵያ ሚዲያዎች ብዙም የዜና ሽፋን የማይሰጠው የአረንጓዴ አሻራ በዓለም ደረጃ ከፍተኛ አድናቆትንና ሽልማት ያስገኘ መሆኑ ይታወሳል። የዘንድሮውን የቅድመ ዝግጅት እና የቀጣይ የስራ አቅጣጫዎች አስመክቶ የብሄራዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ዐቢይ ኮሚቴ የምክክር መድረክ ማካሄዱ ተመልክቷል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ብሄራዊ ዐቢይ ኮሚቴ አስተባባሪ እና የግብርና ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) የመድረኩን አላማ ሲያብራሩ፤ የ2016 ዓ.ም የችግኝ ተከላ የቅድመ ዝግጅት ምዕራፍን መገምገም እና ቀጣይ የስራ አቅጣጫዎች ላይ የጋራ መግባባት ላይ መድረስ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
በ2015 ዓ.ም በተካሄደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያላቸው ችግኞች መተከላቸውንም አስታውሰዋል። ሚኒስትሩ አያይዘውም በተካሄደ የዳሰሳ ጥናት የተተከሉ ችግኞችን በመንከባከብ የጽድቀት መጠናቸውን 90 ከመቶ ማድረስ እንደተቻለም ገልፀዋል፡፡
ለዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር 6 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኝ ለመትከል ዕቅድ መያዙን ጠቅሰው ለዚህም 7 ነጥብ 2 ቢሊየን ችግኝ መዘጋጀቱን ተናግረዋል። በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ለሚተከሉ ችግኞችም በሀገር አቀፍ ደረጃ 1 ነጥብ 2 ሚሊየን ሄክታር መሬት ለተከላ መዘጋጀቱንም ገልጸዋል።
በመጪው ክረምት ለሚካሄደው የችግኝ ተከላ ቀሪ ስራዎች ላይ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል፡፡ የግብርና ሚኒስትሩም ዶ/ር ግርማ አመንቴ ለዐቢይ ኮሚቴው ቀጣይ የስራ አቅጣጫዎች ላይ መመሪያ ሰጥተው፤ የጋራ መግባባት ላይ መደረሱን ከግብርና ሚኒስቴር የተላከው መረጃ ያስረዳል።