\ስድስተኛውን አጠቃላይ አገራዊ ምርጫ የሚታዘቡ የአፍሪካ ሕብረት የረጅም ጊዜ የምርጫ ታዛቢዎች አዲስ አበባ መግባታቸው ተገለጸ። የሕብረቱ የአጭር ጊዜ ታዛቢዎች ከምርጫው አንድ ሳምንት በፊት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጡም ተገልጿል። በቅድመ ምርጫ ግምገማ የተሰማሩ ጉዟቸውን አጠናቀው ከምርጫ ቦርድ ጋር የመጨረሻ ውይይት ያደርጋሉ።
የኢትዮጵያ መንግስት ያቀረበውን ግብዣ ተከትሎ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ሙሳ ፋቂ ማህማት ምርጫውን የሚታዘቡ የአፍሪካ ሕብረት የአጭርና የረጅም ጊዜ ታዛቢዎችን ስምሪት ማድነቃቸው ይታወሳል።
ሕብረቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ ከሕብረቱ አባል አገራት የተውጣጡ ስምንት አባላት ያሉት የረጅም ጊዜ የምርጫ ታዛቢዎች ቡድን ግንቦት 25 እና 26 ቀን 2013 ዓ.ም አዲስ አበባ መግባቱን ገልጿል።
ታዛቢዎቹ በአጠቃላይ ምርጫ ሂደቱ ያለው የፖለቲካ ከባቢ አየር፣ የምርጫው ሕጋዊ ማዕቀፎች፣ የምርጫ ዝግጅትና አስተዳደር ግልጽነትና ውጤታማነት፣ የምርጫ ቅስቅሳ ሁኔታ የመታዘብ ስራ እንደሚያከናውኑም ተጠቅሷል።
ይህ በንዲህ እንዳለ ለቅድመ ምርጫ ግምገማ ወደ ኢትዮጵያ ያቀኑት ተቋማት ቅድመ ምልከታቸውን አጠናቀው ሪፖርታቸውን ለማቅረብ ዛሬ ከምርጫ ቦርድ ጋር የሪፖርት ማሟያ ውይይት እንደሚያደርጉ ተሰምቷል። የኢትይ 12 የአዲስ አበባ ተባባሪ እንዳለው በቅድም ግምገማው ይህ ነው የሚባል የነቀፌታ ችግር እንዳልተገኘ ስራውን እየሰሩ ካሉ ሰምቷል።
አብዛኛው ሕዝብ ምርጫው ተደርጎ መገላገል እንደሚፈልግ፣ ከምርቻው በሁዋላ ሰፊ ተስፋ እንዳላቸውና የምርጫው መጠናቀቅ በጉልህ እንደሚያጠባበቁ የተሰበሰቡ አስተያየቶች እንደሚጠቁሙ የወሬው ምንጮች ገልጸዋል። በአንዳንድ ቦታዎች ረብሻ ይነሳል የሚል ስጋት ያላቸው ቢኖሩም ማን? ለምን? እንዴትና? የት ረብሻ እንደሚያደርግ አያውቁም። በወሬ ደረጃ ግን ሰዎችን የሚያስጨንቁ አሉ።
በብልጽግና ፓርቲ አመራሮች ዘንድ ስጋት እንደማይታይ ታዛቢዎቹ ተረድተዋል። አብዛኞቹ በተዘዋወሩባቸው ስፍራዎች ህዝብ የኮሮና ስጋት እንደሌለበት፤ ለስጋት የሚዳርግ ምንም ጉዳይ አለመኖሩን አይተዋል። ምርጫ ቦርድ ስጋት አለባቸውን ያላቸውን ስፍራዎች በአማራ ክልልና በኦሮሚያ ምርጫ እንዳይካሄድባቸው መወሰኑ ይታወሳል።
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ።… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት
- የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡምየፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የትራንስፖርት ስምሪትና የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር ሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ 11 ግለሰቦች በስር ፍ/ቤት… Read more: የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡም
- መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለየአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ ምክንያቱም “የኢትዮጵያ መንግሥት በሕገ ወጥ መንገድ የአውሮፓ ኅብረት… Read more: መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ
- “ሰራ ሰራ አድርጌ ቶሎ እመለሳለሁ” ሚሊየነሩ የሸኔ የ”ነጻነት” ታጋይ ወደ ጫካ ሲገባ ስንብት ላይ የተናገረውየሚነሳው ጉዳዩ ልብ ሰባሪ ነው፣ ያስቃል፣ ያዝናናል፣ ያስገርማል፣ ያሳዝናል፣ ይቀፋል፣ ያሳፍራል፣ ለማመን ያስቸግራል … አንባቢ ስም… Read more: “ሰራ ሰራ አድርጌ ቶሎ እመለሳለሁ” ሚሊየነሩ የሸኔ የ”ነጻነት” ታጋይ ወደ ጫካ ሲገባ ስንብት ላይ የተናገረው