አሜሪካ በትግራይ ክልል ያለው ችግር እንዲረጋጋ ፍላጎት እንደሌላትና በተቃራኒ ችግሩ እንዲባባስ እያደረገች ነው ስትል ኤርትራ ወቀሳ መሰንዘሯ ተሰምቷል፡፡
የኤርትራው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ትላንት ሰኞ በላከው ደብዳቤ ደብዳቤ እንደገለጸው የባይደን አስተዳደር በትግራይ ክልል ያለው ሁኔታ እንዳይረጋጋ ፍላጎት እንደሌለው መግለጹ ተዘግቧል፡፡
ለዚህም አሜሪካ ላለፉት 20 ዓመታት ለአሸባሪው ህወሃት ቡድን ስታደርግ የነበረውን ድጋፍ በማስታወስ ለችግሩ መከሰት ኤርትራን ተጠያቂ ማድረግም መሰረት የሌለው እንደሆነ ገልጿል፡፡የኤርትራ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦስማን ሳልህ ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት የጻፉት ደብዳቤ አሜሪካ በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ላይ በምታደርገው ጣልቃ ገብነትና እየፈጠረች ባለችው ያልተገባ ጫና ተጨማሪ ችግር እንዲፈጠር እያደረገች መሆኑንና ችግሩ እንዳይቀረፍ እንቅፋት እየሆነች እንደሆነ የሚገልጽ ይዘት ያለው መሆኑን በዘገባው ተገልጿል፡፡
በተጨማሪም ኤርትራ ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት በላከችው ደብዳቤ ላይ አሜሪካ የሽብር ቡድኑ ቀደሞ ወደ ነበረበት ስልጣን ለመመለስ ፍላጎት እንዳላትም መግለጹ ተነግሯል፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ኦስማን ሳልህ የህወሃት ቡድን አሁን ሀገሪቱን እያስተዳደረ ያለውን የዶ/ር አብይ አስተዳደርን በዓለም አቀፉ ማህበረሰቡ ዘንድ አሉታዊ ገጽታ እንዲይዝ የሚያደርጉ የተዛቡ መረጃዎችን በማሰራጨት መወጠሩን ጠቅሰው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤትም ፍትህን ማረጋገጥ የሚያስችሉ እርምጃዎች መውሰድ ይጠበቅበታል ብለዋል፡፡
ሚኒስትሩ አክለውም የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ሰሞኑን በኢትዮጵያና በኤርትራ ባለስልጣናት እና በወታደራዊ ሀላፊዎች ላይ የጣለውን የጉዞ ዕገዳ በተመለከተም ተገቢነት የጎደለው እና በሀገራት የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ የመግባት አንዱ ማሳያ ሲሉ መተቸታቸውን አልጀዚራ በዘገባው አስነብቧል፡፡
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ ወገኖች አስታውቀዋል። ጎን… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ። ለውጭ አገር ሚዲያዎች… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት
- የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡምየፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የትራንስፖርት ስምሪትና የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር ሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ 11 ግለሰቦች በስር ፍ/ቤት የተሰጠውን ዋስትና አፀና።… Read more: የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡም
- መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለየአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ ምክንያቱም “የኢትዮጵያ መንግሥት በሕገ ወጥ መንገድ የአውሮፓ ኅብረት አገራት ውስጥ የሚኖሩ… Read more: መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ
- “ሰራ ሰራ አድርጌ ቶሎ እመለሳለሁ” ሚሊየነሩ የሸኔ የ”ነጻነት” ታጋይ ወደ ጫካ ሲገባ ስንብት ላይ የተናገረውየሚነሳው ጉዳዩ ልብ ሰባሪ ነው፣ ያስቃል፣ ያዝናናል፣ ያስገርማል፣ ያሳዝናል፣ ይቀፋል፣ ያሳፍራል፣ ለማመን ያስቸግራል … አንባቢ ስም ይስጠው። እኔ ስጽፈው… Read more: “ሰራ ሰራ አድርጌ ቶሎ እመለሳለሁ” ሚሊየነሩ የሸኔ የ”ነጻነት” ታጋይ ወደ ጫካ ሲገባ ስንብት ላይ የተናገረው