አሜሪካ በትግራይ ክልል ያለው ችግር እንዲረጋጋ ፍላጎት እንደሌላትና በተቃራኒ ችግሩ እንዲባባስ እያደረገች ነው ስትል ኤርትራ ወቀሳ መሰንዘሯ ተሰምቷል፡፡
የኤርትራው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ትላንት ሰኞ በላከው ደብዳቤ ደብዳቤ እንደገለጸው የባይደን አስተዳደር በትግራይ ክልል ያለው ሁኔታ እንዳይረጋጋ ፍላጎት እንደሌለው መግለጹ ተዘግቧል፡፡
ለዚህም አሜሪካ ላለፉት 20 ዓመታት ለአሸባሪው ህወሃት ቡድን ስታደርግ የነበረውን ድጋፍ በማስታወስ ለችግሩ መከሰት ኤርትራን ተጠያቂ ማድረግም መሰረት የሌለው እንደሆነ ገልጿል፡፡የኤርትራ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦስማን ሳልህ ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት የጻፉት ደብዳቤ አሜሪካ በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ላይ በምታደርገው ጣልቃ ገብነትና እየፈጠረች ባለችው ያልተገባ ጫና ተጨማሪ ችግር እንዲፈጠር እያደረገች መሆኑንና ችግሩ እንዳይቀረፍ እንቅፋት እየሆነች እንደሆነ የሚገልጽ ይዘት ያለው መሆኑን በዘገባው ተገልጿል፡፡
በተጨማሪም ኤርትራ ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት በላከችው ደብዳቤ ላይ አሜሪካ የሽብር ቡድኑ ቀደሞ ወደ ነበረበት ስልጣን ለመመለስ ፍላጎት እንዳላትም መግለጹ ተነግሯል፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ኦስማን ሳልህ የህወሃት ቡድን አሁን ሀገሪቱን እያስተዳደረ ያለውን የዶ/ር አብይ አስተዳደርን በዓለም አቀፉ ማህበረሰቡ ዘንድ አሉታዊ ገጽታ እንዲይዝ የሚያደርጉ የተዛቡ መረጃዎችን በማሰራጨት መወጠሩን ጠቅሰው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤትም ፍትህን ማረጋገጥ የሚያስችሉ እርምጃዎች መውሰድ ይጠበቅበታል ብለዋል፡፡
ሚኒስትሩ አክለውም የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ሰሞኑን በኢትዮጵያና በኤርትራ ባለስልጣናት እና በወታደራዊ ሀላፊዎች ላይ የጣለውን የጉዞ ዕገዳ በተመለከተም ተገቢነት የጎደለው እና በሀገራት የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ የመግባት አንዱ ማሳያ ሲሉ መተቸታቸውን አልጀዚራ በዘገባው አስነብቧል፡፡
- የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ“ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ” እያሉ በስሟ ሲምሉ የነበሩ ብዙዎች ነበሩ፤ ከልባቸው ለቃላቸው ታምነው ልጅ የሆኗት ግን ጥቂቶች ብቻ ናቸው። አንዳንዶች በስሟ… Read more: የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ
- አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ“ወገኖቼ እንማርና እናስተምር፣ ወንጀልን እንጸየፈው፣ እንጥላው፣ ወንጀልን ተጸይፈን ወንጌልን እንውደደው፣ በወንጌል እንኑር፣ ወንጌል ሕጓም ስርዓቷም ያማረች ናት፤ ወንጌላዊ መኾን… Read more: አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ
- ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናውቤት የተባለች አንዲት ሴት እንዲህ ብላለች፦ “ደም ማነስ የያዘኝ በአሥራዎቹ ዕድሜ ሳለሁ ነው። ቶሎ ይደክመኝ፣ አጥንቶቼን ይቆረጥመኝ፣ እንዲሁም ትኩረቴ… Read more: ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናው
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ ወገኖች አስታውቀዋል። ጎን… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ። ለውጭ አገር ሚዲያዎች… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት