በገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ የተመራ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የልዑካን ቡድን ከጅቡቲ ፕሬዝዳንት እስማዔል ዑመር ጉሌህ ጋር ተወያየ።
በገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሺዴ የተመራና የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የጦር ኃይሎች ኢታማዦር ሹም ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ እንዲሁም የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጄኔራል አቶ ተመስገን ጥሩነህን ያካተተ የመንግስት ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ከጅቡቲው ፕሬዝዳንት ክቡር እስማዔል ኡመር ጌሌህ ጋር ተገናኝተው በወቅታዊ አካባቢያዊና በሁለቱ አገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡
በውይይቱም የሁለቱ አገራት ስትራቴጂካዊ ግንኙነት ታሪካዊ፣ የማይለዋወጥና በማናቸውም የውጭ ኃይል ተፅዕኖ የማይናወጥ መሆኑ ተነስቷል።
የህዘብ ለህዝብ ትሥሥራቸውም በባህልና ቋንቋ ጭምር የተሳሰረና በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑም ተገልጿል፡፡
የልዑካን ቡድኑ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታዎች ዙሪያ ለፕሬዝዳንቱ ማብራሪያ የሰጠ ሲሆን÷ በመንግስት በኩል በአገር ውስጥም ሆነ ከውጭ የሚፈጠሩ ችግሮችን በመቋቋም የአገሪቱን ሰላም ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን አብራርቷል።
በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል በተለይም በትግራይ ክልል የህብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት የማረጋገጥ፣ ሰብዓዊ ድጋፎችንም አጠናክሮ የማስቀጠልና መደበኛ የትምህርትና የግብርና ሥራዎችም እንዲጀመሩ የተደረገበት አግባብ መኖሩም ነው የተገለጸው፡፡
የጅቡቲው ፕሬዝዳንት እስማዔል ኡመር ጌሌህ በበኩላቸው÷በኢትዮጵያና ጅቡቲ መካከል ያለው ግንኙነት ከመቼውም ጊዜ በላይ የተጠናከረ መሆኑን ገልጸዋል።
የሁለቱ ሀገራት ግንኙነትም ታሪካዊ፣ ጠንካራና በማናቸውም የውጭ ተፅዕኖ የማይናወጥ መሆኑንም አረጋግጠዋል፡፡
ጅቡቲ ኢትዮጵያ የውስጥ ችግሮቿን ለመፍታት እያደረገች ያለውን ጥረት አድንቀው÷ የሁለቱ አገራት ትስስር ጠንካራ እንደሆነና መለያየት በማይችል መልኩ የተሳሰረ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በአንዱ አገር ውስጥ የሚፈጠር ችግር ሌላውም ላይ ተፅዕኖን እንደሚያሳድር ፕሬዝዳንቱ በውይይቱ ወቅት አንስተዋል ፡፡
በመሆኑም ትሥሥሩን ይበልጥ ለማጠናከር ጅቡቲ ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ መሆኗን ለልዑካን ቡድኑ አረጋግጠዋል፡፡
ከዚሁ ጋር ተያይዞ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መከላከያ ኢታማጆር ሹም ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ ከጅቡቲው አቻቸው ጄኔራል ዘካሪያ ጋር ተገናኝተው በሁለቱ የመከላከያ ኃይሎች መካከል ያለውን ትብብር ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ዙሪያ ተወያተዋል፡፡
በውይይቱ ወቅት በኢትዮጵያና ጅቡቲ መካከል ያለው የህዝብ ለህዝብና የመንግስታቱ ግንኙነት ጠንካራ መሆኑን አንስተው ይህንኑ ግንኙነት በወታደራዊ መስክም ማስቀጠል እንደሚገባ ተወያዮቹ አንስተዋል፡፡
በዚሁ መሠረት በወታደራዊ መስክ የመረጃ ልውውጥ፣ የትምህርትና ስልጠና ትብብር እንዲሁም የልምድ ልውውጦችን ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡
በሁለቱ አገራት የጋራ ድንበርና የኢትዮ-ጅቡቲ ኮሪደርን ሰላማዊ ቀጠና ከማድረግ አኳያም በትብብር እንደሚሠሩ የተወያዩ ሲሆን በዓመት አንድ ጊዜ የሚካሄድ የጋር ሁለትዮሽ ውይይቶችንም አጠናክረው ለማስቀጠል ከስምምነት ላይ መድረሳቸውን ጅቡቲ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
- የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ“ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ” እያሉ በስሟ ሲምሉ የነበሩ ብዙዎች ነበሩ፤ ከልባቸው ለቃላቸው ታምነው ልጅ የሆኗት ግን ጥቂቶች ብቻ ናቸው።… Read more: የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ
- አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ“ወገኖቼ እንማርና እናስተምር፣ ወንጀልን እንጸየፈው፣ እንጥላው፣ ወንጀልን ተጸይፈን ወንጌልን እንውደደው፣ በወንጌል እንኑር፣ ወንጌል ሕጓም ስርዓቷም ያማረች ናት፤… Read more: አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ
- ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናውቤት የተባለች አንዲት ሴት እንዲህ ብላለች፦ “ደም ማነስ የያዘኝ በአሥራዎቹ ዕድሜ ሳለሁ ነው። ቶሎ ይደክመኝ፣ አጥንቶቼን ይቆረጥመኝ፣… Read more: ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናው
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ ወገኖች… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ። ለውጭ… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት