Site icon ETHIO12.COM

የኢትዮጵያ ኢ-ቪዛ (E-Visa) እና በመዳረሻ በሚሰጥ ቪዛ (Visa on Arrival) አገልግሎት ቆሟል ?

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ትናንት ምሽት በይፋዊ ድረ-ገፁ ላይ እንዳሰፈረው ከኢሚግሬሽን ቢሮ በመጣ መመርያ መሰረት የE-Visa እና Visa on Arrival አገልግሎቶች ከአርብ እኩለ-ለሊት ጀምሮ ለግዜው አይሰጡም።

ይህ ግን የትራንዚት መንገደኞችን እንደማይመለከት አክሎ ገልጿል።

የኢሚግሬሽን ድረ-ገፅ ደግሞ የ E-Visa ድረ-ገፁ እድሳት ላይ እንዳለ ገልፆ ተገልጋዮች ለቪዛ ጉዳዮች በአቅራቢያቸው ወደሚገኝ ኤምባሲ ወይም ቆንፅላ ቢሮ እንዲያመሩ ይመክራል።

በዚህ ዙርያ ኢሚግሬሽን ዛሬ ጥዋት ለኢትዮጵያ ቼክ በሰጠው ቃል አገልግሎቱ የተቋረጠው በድረ-ገጹ ላይ የማሻሻያ ስራ እየተከናወነ በመሆኑ ነው።

የማሻሻያ ስራው በቅርቡ ይጠናቀቃል ሲል ገልጿል።

በዚህም መሰረት የ E-Visa ያላቸው እንዲሁም Visa on Arrival የሚፈልጉ ተጓዦች ወደ ኢትዮጵያ የሚደረግ የአየር ጉዞን ማድረግ አይችሉም፣ አየር መንገዶችም አያሳፍሩም።

ይህም ማለት ፦

ይህ ጉዳይ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ብቻ ሳይሆን ሁሉም ወደ ኢትዮጵያ በረራ የሚያደርጉ አየር መንገዶችን ይመለከታል።

ኢትዮጵያቼክ via @tikvahethiopia

Exit mobile version