አሸባሪ የህወሃት ቡድን በራያና አዘቦ ”የለውጥ ደጋፊዎች ናችሁ” በሚል ንጹሃን ዜጎችን እየገደለ መሆኑን የራያ ራዩማ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ጽህፈት ቤትና የውጭ ግንኙነት ሀላፊ ጌታቸው ከበደ ገለጹ፡፡
ባላቸው ስጋት ምክንያት ከአስር ሺህ በላይ ነዋሪዎች ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸውንም ገልጸዋል።
ኢዜአ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ከትግራይ ክልል መልቀቅ ተከትሎ በራያ አካባቢ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ ምን እንደሚመስል ከአቶ ጌታቸው ከበደ ቆይታ አድርጓል፡፡
የፌዴራል መንግስት በትግራይ ክልል የተናጠል የተኩስ ማቆም ውሴ መወሰኑን ተከትሎ አሸባሪ የህወሃት ቡድን ”የለውጥ ደጋፊ ናችሁ” በሚል ከፍተኛ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ጉዳት ማድረሱን አቶ ጌታቸው ከበደ ተናግረዋል፡፡
ቡድኑ ንጹሃንን እየገደለ፣ ቤትና ንብረቶችን በማውደም ራያ አዘቦ ተብሎ በሚታወቀው መሆኒ፣ መቻሬ፣ ጨርጨር እና ሓደ አልጋ በታባሉ አካባቢዎች በሰው ህይወትና በንብረት ላይ ከባድ ጉዳት ማድረሱን ተናግረዋል፡፡
ሽብርተኛ ቡድኑ ቀደም ሲል መከላከያ ወደ አካባቢው በገባበት ወቅት አቀባበል ያደረጉ፣ ስንቅ ያቀረቡ፣ ለሰራዊቱም የባህል ልብስ ያለበሱ ናቸው በሚል በሻይ መሸጥ የሚተዳደሩ፣ የባህል ልብስ የሚሰሩ፣ በጫማ ማጽዳት ስራ የተሰማሩ ደሃ ሰዎችን በግፍ በመግደል የጥፋት ስራዎችን መስራቱን አመላክተዋል፡፡
በዚህም በአካባቢው እየተፈጠረ ባለው ችግር ስጋት ምክንያት ከአስር ሺህ በላይ የሚቆጠሩ ነዋሪዎች መከላከያ ባለባቸው የራያ የገጠር እና የከተማ አካባቢዎች በርታህላ፣ ታኦ፣ ዳዩ፣ አላማጣ፣ እንዲሁም ራያ ቆቦ ከተማ ጭምር ተጠልለው ይገኛሉ ብለዋል፡፡
አሸባሪው የህወሃት ቡድን ”እናስተምራችዋለን” በሚል ሰበብ በርካታ ወጣቶችን በሲኖ ትራክ መኪና ጭነው በመውሰድ ኢ ሰብዓዊ ድርጊት እየፈጸሙባቸው መሆኑንም ተናግረዋል።
የለውጥ ደጋፊዎች ናችሁ በሚል የጊዜያዊ አስተዳደር አባላት እና የነዋሪዎች መኖሪያ የሆኑ ከአራት መቶ በላይ ቤቶችን መቃጠላቸውን ገልጸዋል።
በትግራይ ክልል መቀሌ እና በሌሎች ከተሞች ከጊዜያዊ አስተዳደሩ እና መከላከያን ተባብራችኋል ያላቸውን ንጹሐን ላይ ግድያ እየፈጸመ እንደሚገኝ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ ገልጿል።
- ምን ያክል ተዘጋጅተናል? ጥድፊያ አገር አልባ ለመሆን !! ህጻናቱ ምን አጠፉ?ያለፈውን ግማሽ ምዕተ ዓመት የኢትዮጵያ ፖለቲካ እና ሥነ መንግሥት ታሪክ በጥሞና የተከታተለ ኢትዮጵያዊ የግዛት አንድነቷን እና የፖለቲካ ነጻነቷን… Read more: ምን ያክል ተዘጋጅተናል? ጥድፊያ አገር አልባ ለመሆን !! ህጻናቱ ምን አጠፉ?
- የደም ግፊት በመለካትና ክትትል በማድረግ የስትሮክ ተጋላጭነትን መቀነስአንድ ሰው የደም ግፊት መጠኑ ከፍተኛ ከሆነ እና በጊዜው ሕክምና ካላደረገ ለከፍተኛ የልብ በሽታና በደም ዝውውር ማነስ ምክንያት… Read more: የደም ግፊት በመለካትና ክትትል በማድረግ የስትሮክ ተጋላጭነትን መቀነስ
- የስኳር ህመም አይነቶች እና ምልክቶችየስኳር ህመም በደም ውስጥ የስኳር መጠን ከሚገባው በላይ ሆኖ በሚገኝበት ሰዓት የሚከሰት ተላላፊ ያልሆነ የህመም አይነት ነው። በዋናነት… Read more: የስኳር ህመም አይነቶች እና ምልክቶች
- ማንኮራፋትና ትዳርን እስከ ማፍረስ የሚያደርሰው መዘዙ ? ማንኮራፋት መፍትሄ አለው?የማንኮራፍት መዘዙ እንቅልፍ ማሳጣት ብቻ አይደለም። ማንኮራፋት ከሚያንኮራፉት ሰዎች ጎን በሚተኙ ሰዎች አካላዊ እና አእምሮ ጤና ላይ ጉዳት… Read more: ማንኮራፋትና ትዳርን እስከ ማፍረስ የሚያደርሰው መዘዙ ? ማንኮራፋት መፍትሄ አለው?
- Ethiopia Working To Secure New Development Bank MembershipThe Ministry of Foreign Affairs disclosed that Ethiopia is working hard to become member of BRICS’ New Development… Read more: Ethiopia Working To Secure New Development Bank Membership