ሁለቱ አገራት ግንኙነታቸውና በወታደራዊ መስክ ያላቸው ውለታ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይና ምክትላቸው ደመቀ መኮንን ፕሬዚዳንት ፑቲንን ካናገሩ በሁዋላ ይበልጥ ማደጉ ተወስቷል። ውይይቱ ወታደራዊ ቴክኒክ ድጋፍ መስጠትን አስመልክቶ አጀንዳ አጽድቆ ውይይቱን መጀመሩን ኢቢሲ አስታውቋል።
የሁለቱን ሀገሮች ወታደራዊ ትብብር ማጠናከርን ዓላማ ያደረገው 11ኛው የኢትዮ – ሩሲያ ወታደራዊ የቴክኒክ ትብብር የጋራ ውይይት በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ነው። ውይይቱ 10ኛውን የወታደራዊ ቴክኒክ ፕሮግራም አጀንዳ በማጽደቅ መጀመሩን ተነግሯል።
በመኮንኖች ክበብ እየተካሄደ የሚገኘው ምክክር፣ የኢትዮጵያን እና የሩሲያን ወታደራዊ ቴክኖሎጂ ፣ ክህሎት እና እውቀት ማሳደግ ላይ ያተኮረ ነው፡፡
በመክፈቻው ስነ-ስርዓት ላይ ንግግር ያደረጉት የመከላከያ ፋይናንስ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ማርታ ሉዊጂ ፣ ሁለቱ ሀገሮች ከ1898 ጀምሮ በዲፕሎማሲ፣ በወታደራዊ ፣ በኢኮኖሚ ፣ በፖለቲካ እና በማህበራዊ መስክ ታሪካዊና ጠንካራ ግንኙነት ሲያደርጉ መቆየታቸውን አስታውሰዋል፡፡
በአሁኑ ወቅትም ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ተገናኝተው ከመከሩ ወዲህ የሁለቱ ሀገሮች ግንኙነት በጣም ጥብቅ እየሆነ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡
ኢትዮጵያ የህግ ማስከበር ዘመቻ ስታደርግ ሩሲያ የውስጥ ጉዳያችን እንደሆነ አቋም ይዛ በመንቀሳቀሷ፣ ባደረግነው 6ኛው ምርጫ፣ በታላቁ ህዳሴ ግድብና በሌሎችም ሀገራዊ ጉዳዮች ከኢትዮጵያ ጎን ቆማ ወዳጅነቷን በማሳየቷ ሚኒስትር ዴኤታዋ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
የዚህን ስብሰባ ውጤትንም የሁለቱን ሀገሮች የጋራ ተጠቃሚነት በሚያረጋግጥ መልኩ ተግባራዊ እንደሚደረግ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡
በሩሲያ ፌዴሬሽን የወታደራዊ የቴክኒክ ትብብር ምክትል ዳይሬክተር ፑንቹክ አናቶሊ፣ የቆየ ወዳጅነት አለን፤ በወታደራዊ መስክ ብዙ የኢትዮጵያ መከላከያ አባላት በሩሲያ ስልጠና ወስደዋል፤ ይህ ስብሰባም የሁለቱን ሀገሮች የቆየ ወዳጅነት የሚያሳድግ እንደሚሆን አመልክተዋል።
የመከላከያ ኢንዱስትሪ እና ደጀን አቭዬሽንን የቴክኖሎጂ አቅም ለማሳደግ እየተደረገ ያለውን ስራ በጋራ እንደሚያጎለብቱም መናገራቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
በኢትዮጵያ በኩል የመከላከያ ፋይናንስ ዘርፍ ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፣ አየር ሀይል እና የመከላከያ ኢንዱስትሪ ዘርፍ በውይይቱ ተሳታፊ ሲሆኑ ፣ በሩሲያ በኩሉ ደግሞ ፣ በኢትዮጵያ የሩሲያ ባለ ሙሉ ስልጣን አምባሳደር ተሬከሂን ኢቭጌኒ እንዲሁም በሩሲያ መከላከያ ቴክኒካል ዘርፍ ላይ የሚሰሩ ተቋማት የስራ ሀላፊዎች፣ ኤክስፐርቶች እና ሌሎች አባላት መሳተፋቸው ታውቋል።
- Are Tigray mercenaries fighting in conflict-ravaged Sudan?Mercenaries from Ethiopia’s Tigray People’s Liberation Front are fighting alongside Sudanese army regulars against fighters of the Rapid Support Forces (RSF), the paramilitary… Read more: Are Tigray mercenaries fighting in conflict-ravaged Sudan?
- Sudan’s RSF Accuse Tigray People’s Liberation Front of Backing SAFSudanese warring party Rapid Support Forces has officially accused the Tigray People’s Liberation Front Fighters of fighting in Sudan in support of the… Read more: Sudan’s RSF Accuse Tigray People’s Liberation Front of Backing SAF
- የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ“ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ” እያሉ በስሟ ሲምሉ የነበሩ ብዙዎች ነበሩ፤ ከልባቸው ለቃላቸው ታምነው ልጅ የሆኗት ግን ጥቂቶች ብቻ ናቸው። አንዳንዶች በስሟ የሚገዘቱት እንጀራዋን ለመብላት እንጂ… Read more: የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ
- አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ“ወገኖቼ እንማርና እናስተምር፣ ወንጀልን እንጸየፈው፣ እንጥላው፣ ወንጀልን ተጸይፈን ወንጌልን እንውደደው፣ በወንጌል እንኑር፣ ወንጌል ሕጓም ስርዓቷም ያማረች ናት፤ ወንጌላዊ መኾን መልካም ነው፣ ወንጀለኛ መኾን… Read more: አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ
- ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናውቤት የተባለች አንዲት ሴት እንዲህ ብላለች፦ “ደም ማነስ የያዘኝ በአሥራዎቹ ዕድሜ ሳለሁ ነው። ቶሎ ይደክመኝ፣ አጥንቶቼን ይቆረጥመኝ፣ እንዲሁም ትኩረቴ በቀላሉ ይከፋፈል ነበር። ሐኪሜ… Read more: ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናው