የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር ዕርዳታን ለጦርነት እንዴት እንደተጠቀመበት የሚያውቁ ዜጎች ዛሬም መንግስት ከደረግ ስህተት በመማር ለአፍታም ቸል እንዳይል ጥሪ እያሰሙ ነው። በእርዳታ ስም የገቡ ድርጅቶቻቸው አቋማቸውና አካሄዳቸው የማይምር መሆኑንን የሚያሳዩ ምልክት በመታየታቸው አንዳንዶች ስጋት እንዳላቸውም እየጠቀሱ ነው።
በማህበራዊ ሚዲያ፣ በተለያዩ አውዶችና በጎንዮሽ ሕዝብ ” የእርዳታ ቁሳቁስ ሊፈተሽ ይገባል። መፈተሽ ከደህንነታችን አንጻር ለነገ የሚባል አይደለም። ለጋሾችም ቢሆኑ ፍተሻን የሚቃወሙበት አንዳች ህጋዊ መሰረት የላቸውም” ብለዋል። ኢዜአ ያነፋገራቸው ባለሙያ የሚከተለውን ብለዋል።
የተራድኦ ድርጅቶች ከተፈቀደላቸው ተግባር ውጭ እንዳይንቀሳቀሱ መንግስት ጥብቅ ቁጥጥር ማድረግ እንዳለበት የህግና የታሪክ ምሁር ዶክተር አልማው ክፍሌ ተናገሩ።የተራድኦ ድርጅቶች ከአድሎ በጸዳ መልኩ ሰብዓዊነት፣ ገለልተኝነትና ነጻነታቸውን ጠብቀው በችግር ውስጥ ያሉ ሰዎችን ለመርዳት የተቋቋሙ ናቸው።
ዓለም አቀፋዊ የሰብዓዊ ድርጅቶች ደግሞ በየትኛውም የዓለም ጥግ ያሉ አገሮች ተፈጥሯዊም ሆነ ሰው ሰራሽ ችግሮች ወይም ግጭት ሲገጥማቸው ድጋፍ ለማድረግ ይገባሉ።በኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርስቲ የህግና የታሪክ ምሁር ዶክተር አልማው ክፍሌ፤ አገሮች ቀውስ በሚገጥማቸው ጊዜ የተራድኦ ድርጅቶች የሚያደርጓቸው ሰብዓዊ ድጋፎች ትልቅ ፋይዳ እንዳላቸው ያስረዳሉ።ነገር ግን እነዚህ ድርጅቶች በአንድ አገር ውስጥ ለሰብዓዊ ድጋፍ ሲንቀሳቀሱ መከተል የሚጠበቅባቸው መብቶችና ግዴታዎች መኖራቸውን ተናግረዋል።
የተራድኦ ድርጅቶቹ ሥራቸውን ሲያከናውኑ የአገር ሉዓላዊነትን ባከበረ መልኩ መሆን እንዳለበት አመልክተው፤ በውስጣዊ ፖለቲካ እንዲሁም ህዝብንና አገርን ከሚጎዱ እንቅስቃሴዎች መታቀብ እንዳለባቸውም አንስተዋል።መንግስት በትግራይ የወሰደውን የህግ ማስከበር እርምጃ ተከትሎ ዓለም አቀፍ የተራድኦ ድርጅቶች ወደ አካባቢው መግባታቸውን ጠቅሰው፤ የድርጅቶቹ ሰራተኞች ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ተገቢ ባለሆነ እንቅስቃሴዎች ውስጥ እየታዩ መሆኑን ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅት አንዳንድ የተራድኦ ድርጅት አባላቶች ተገቢ ባልሆነ መልኩ በህዝብና መንግስት ላይ የሽብር እንቅስቃሴን አንግበው ለሚንቀሳቀሱ ሃይሎች የመወገን አዝማሚያ እንደሚታይም ጠቅሰዋል።በአሸባሪነት የተፈረጀው ድርጅት አባላት በተራድኦ ድርጅቶች ቅጥር ግቢ ውስጥ ሲንቀሳቀሱ በማህበራዊ ሚዲያዎች መሰራጨቱንም ለአብነት አንስተዋል።
አሸባሪው “ህወሃት ደርግን ለመጣል ባደረገው የትጥቅ ትግል የተራድኦ ድርጅቶች የጦር መሳሪያ በማቀበል ሲያግዙ ነበር” ያሉት የህግና ታሪክ ምሁሩ፤ መንግስት ከደርግ ዘመን ሂደቶች ትምህርት በመውሰድ የተራድኦ ድርጅቶች የሚያደርጉትን ያልተገባ እንቅስቃሴ መከታተል እንዳለበት ገልጸዋል።በእርዳታ ስም ሌሎች የአገሪቱን ህግ የሚጥሱ ተግባራት እንዳይከናወኑ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ ገልጸው፤መንግስት አስፈላጊውን ፍተሻ የማድረግና እርዳታው ለተገቢው አካል መድረሱን ማረጋጋጥ እንዳለበትም ተናግረዋል።መንግስት ግብረ ሃይል በማቋቋም የቁጥጥር ስራውን ማከናወን እንደሚችልም ዶክተር አልማው ተናግረዋል።
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ ወገኖች አስታውቀዋል። ጎን ለጎን የትግራይ ከፍተኛ ባለስልጣናትና የዞን… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ። ለውጭ አገር ሚዲያዎች ዜና የሚያቀብሉና እነሱኑ የሚከተሉ ስምምነቱ… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት
- የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡምየፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የትራንስፖርት ስምሪትና የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር ሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ 11 ግለሰቦች በስር ፍ/ቤት የተሰጠውን ዋስትና አፀና። ፍርድ ቤቱ ተጠርጣሪዎቹ ከሀገር እንዳይወጡ… Read more: የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡም
- መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለየአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ ምክንያቱም “የኢትዮጵያ መንግሥት በሕገ ወጥ መንገድ የአውሮፓ ኅብረት አገራት ውስጥ የሚኖሩ ዜጎቹን መልሶ ለመቀበል ያሳየው ተባባሪነት… Read more: መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ
- “ሰራ ሰራ አድርጌ ቶሎ እመለሳለሁ” ሚሊየነሩ የሸኔ የ”ነጻነት” ታጋይ ወደ ጫካ ሲገባ ስንብት ላይ የተናገረውየሚነሳው ጉዳዩ ልብ ሰባሪ ነው፣ ያስቃል፣ ያዝናናል፣ ያስገርማል፣ ያሳዝናል፣ ይቀፋል፣ ያሳፍራል፣ ለማመን ያስቸግራል … አንባቢ ስም ይስጠው። እኔ ስጽፈው ግን በሃፍረት ስሜት ነው። ያፈርኩት… Read more: “ሰራ ሰራ አድርጌ ቶሎ እመለሳለሁ” ሚሊየነሩ የሸኔ የ”ነጻነት” ታጋይ ወደ ጫካ ሲገባ ስንብት ላይ የተናገረው