አቶ ጌታቸው ረዳ ” ወደ ደብረብርሃን ወይስ ጎንደር” ሲሉ ወዳሻቸው የሽር ሽር ያህል እንደሚያቀኑ ባስታወቁ በሃያ አራት ሰዓት ውስጥ ቆቦን መነተቃቸው ተሰማ። በአፋር ግንባር ከፈተኛ ቁጥር ያላቸው ምልምሎች መማረካቸው ታወቀ።
የአሸባሪው ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው እንዳሉት እሳቸው የሚወክሉት ጦር ወደ ፈለገው አቅጣጫ ለመሄድ የሚገድበው አንዳች ሃይል የለም። መደራደር እንደሚፈልጉ የሚነገርላቸው ጄነራል ጻድቃንም ” ወደ አዲስ አበባ ለመገስገስ የምያግድ አንዳችም ነገር የለም” የሚል ቃለ ምልልስ አድርገዋል።
ዛሬ ረፋዱ ላይ የሚወጡ መረጃዎች እንደሚያመለቱት ትህነግ ቆቦን ከሙሉ ኪሳራ ጋር ተነጥቋል። በአፋር ግንባር ሰፊ ቦታ የሚሸፍን ጦርነት ለመክፈት ሲያጋግዛቸው የነበሩ ምልምል ወታደሮች ከመኪና ሳይወርዱ ተይዘዋል። ከአካባቢው ምስክሮች መረዳት እንደተቻለው የተያዙት ከመኪና ሳይወርዱ በመሆኑ ” ተማረኩ” ሊባል አይችልም።
ከተማረኩት በተጨማሪ በሺህ የሚቆጠሩ መደምሰሳቸውን በስፍራው ያሉ ምስክሮች ገልጸዋል። የጅቡቲ ባቡርና የየብስ መንገድ እንደሚቆርጡ ከሳምንት በፊት የተነገረላቸው የትግነግ ተዋጊዎች እስካሁን በአፋር ግንባር ይህ ነው የሚባል ማስመዝገባቸውን አልተቆሙም።
የጦርነት መረጃ ሁሉ እንደማይነገር የሚገልጸው መንግስት የመከላከያ ሃይል ከድካምና ከባይተዋርነት አገግሞ ሰንጋ እየበላ ደጀን መካከል ሆኖ መዋጋት ከጀመረ አንስቶ በትህነግ ላይ ከፈተኛ የሚባል ሰባዊ ቀውስ እያደረሰ ነው።
ለደጋፊዎቻቸው ብርታት ሰፊ የፕሮፓጋንዳ ድል ዘመቻ የሚያስተጋቡት የትህነግ ደጋፊዎች በተመሳሳይ ” ትግራይ እያለቅች ነው” የሚል የማህበራዊ ዘመቻ ጀምረዋል። በተመሳሳይ ትህነግ አሸባሪ መሆኑንን የሚያበስር ሎጎ ኢትዮጵያን የሚወዱ ዜጎች እያሰራጩ ነው።
ትህነግ ቆቦን መያዙን ሲያስታውቅ ካሰራጨው ፎቶ በተለይ ቆቦን ስለመነጠቁ ለደጋፊዎቹ ያለው ነገር የለም። በግንኙነት መረጃውን ከመስማት ውጪ መንግስት ቆቦ ስለመያዟም ሆነ ስለመለቀቋ ያለው ነገር የለም። አቶ ተሻገር ዛሬ ባሰሙት የክተት ጥሪ ‘ ስለወታደራዊ ውሎ በዚህ ገባን ወጣን እያልን መናገር አያስፈልግም። ይህን አሸባሪ ግን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እናተፋዋለን ” ማለታቸው ይታወሳል።
መከላከያ አሁን ላይ በትግራይ ክልል ውስጥ ገብቶ መዋጋት ያቆመ ሲሆን የትህነግ ሃይል ሊያተቃ ሲመጣ አፈግፍጎ አመቺ ቦታ ላይ ሲደርሱ በሂሊኮፕተር እያሳደዱ እንደሚመታቸው መረጃዎች ይጠቁማሉ።
- መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለየአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ ምክንያቱም “የኢትዮጵያ መንግሥት በሕገ ወጥ መንገድ የአውሮፓ ኅብረት አገራት ውስጥ የሚኖሩ ዜጎቹን መልሶ ለመቀበል ያሳየው ተባባሪነት… Read more: መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ
- “ሰራ ሰራ አድርጌ ቶሎ እመለሳለሁ” ሚሊየነሩ የሸኔ የ”ነጻነት” ታጋይ ወደ ጫካ ሲገባ ስንብት ላይ የተናገረውየሚነሳው ጉዳዩ ልብ ሰባሪ ነው፣ ያስቃል፣ ያዝናናል፣ ያስገርማል፣ ያሳዝናል፣ ይቀፋል፣ ያሳፍራል፣ ለማመን ያስቸግራል … አንባቢ ስም ይስጠው። እኔ ስጽፈው ግን በሃፍረት ስሜት ነው። ያፈርኩት… Read more: “ሰራ ሰራ አድርጌ ቶሎ እመለሳለሁ” ሚሊየነሩ የሸኔ የ”ነጻነት” ታጋይ ወደ ጫካ ሲገባ ስንብት ላይ የተናገረው
- ሕገ ወጥ የጦር መሳሪያና የደኅንነት ስጋት – አቅራቢ፣ ፈላጊ፣ ነጋዴ፣ ደላላ ተገናኙና መደበኛ ገበያ ሆነ!በፖለቲካም ሆነ በአካባቢያዊ አጀንዳ ነፍጥ ያነገቡ እና ጦርነትን አማራጭ አድርገው የሚንቀሳቀሱ ኢ -መደበኛ አደረጃጀቶች ሁሉ የጦር መሳሪያ ፍላጎት ይኖራቸዋል፡፡ የጦር መሳሪያ ፍላጎት ሲኖር መሳሪያ… Read more: ሕገ ወጥ የጦር መሳሪያና የደኅንነት ስጋት – አቅራቢ፣ ፈላጊ፣ ነጋዴ፣ ደላላ ተገናኙና መደበኛ ገበያ ሆነ!
- ምን ያክል ተዘጋጅተናል? ጥድፊያ አገር አልባ ለመሆን !! ህጻናቱ ምን አጠፉ?ያለፈውን ግማሽ ምዕተ ዓመት የኢትዮጵያ ፖለቲካ እና ሥነ መንግሥት ታሪክ በጥሞና የተከታተለ ኢትዮጵያዊ የግዛት አንድነቷን እና የፖለቲካ ነጻነቷን በአንጻሩ ጠብቃ የኖረች ሀገር፤ ከአሁን በኋላ… Read more: ምን ያክል ተዘጋጅተናል? ጥድፊያ አገር አልባ ለመሆን !! ህጻናቱ ምን አጠፉ?
- የደም ግፊት በመለካትና ክትትል በማድረግ የስትሮክ ተጋላጭነትን መቀነስአንድ ሰው የደም ግፊት መጠኑ ከፍተኛ ከሆነ እና በጊዜው ሕክምና ካላደረገ ለከፍተኛ የልብ በሽታና በደም ዝውውር ማነስ ምክንያት ለሚከሰት የአዕምሮ ሥራ መታወክ (ስትሮክ) የመጋለጥ… Read more: የደም ግፊት በመለካትና ክትትል በማድረግ የስትሮክ ተጋላጭነትን መቀነስ