ማንኛውም የተቀመጠውን መመሪያ የሚጥስ የአውሮፕላን አብራሪም ሆነ ኦፕሬተር ለሚደርሰው አደጋ ሃላፊነት እንደሚወስድ የወቅታዊ ሁኔታ መረጃ ማጣሪያ አስጠንቅቋል፡፡
Ethiopia Current Issues Fact Check የወቅታዊ ሁኔታ መረጃ ማጣሪያ በማህበራዊ ትስስስ ገጹ ላይ ባሰፈረው ጽሁፍ፣ ቀደም ሲል ሰኔ 23 ቀን 2013 ዓ.ም የአየር በረራ መረጃ ማሳወቂያ (NOTAM& AIP SUP) ቁጥር A0166/21 እና AIP SUP A04 ,2021) መተላለፉን አስታውሷል፡፡
በተላለፈው መመሪያ መሠረትም ማንኛውም የአውሮፕላን አብራሪም ሆነ ኦፕሬተር የተቀመጠውን መመሪያ ከጣሰ ለሚደርሰው አደጋ ሃላፊነቱ የራሱ የጣሰው አካል መሆኑንን መግለጫው አስታውቋል።በስምምነቱና ማስታወቂያው መስረት በኮድና በቁጥር ተሰፍሮ በቀረበው ማሳወቂያ፣ መንግስት ይህን በማያከብሩ ላይ ለሚወሰደው እርምጃ ሃላፊነት እንደማይወስድ ለምን እንዳስታወቀ ምክንያቱን አላብራራም።
በማስታወሻው በይፋ ባይገለጽም በርዳታ ስም በቀጥታ ወደ ትግራይ በረራ እንዲደረግ ተደጋጋሚ ጥያቄ መቅረቡ ይታወሳል። መንግስት ጥያቄውን ተቀብሎ፣ ትብብር እንደሚያድርግ አስታውቆ እንዳለው ” ማንኛውም በረራ አዲስ አበባ አውሮፕላን ማረፊያ ደርሶ ፍተሻ እንዲደረገበት በተደረሰው ስምምነት መሰረት የሚከናወን ነው። በዚሁ መግባቢያ መሰረት የዓለሙ የምግብ ድርጅት አውሮፕላን ከአንዴም ሁለቴ አስፈላጊው ፍተሻ ተደርጎበት መቀለ ደርሶ መመለሱ መዘገቡ ይታወሳል።
ስምምነቱ ይህ ሆኖ ሳለ ለምን መንግስት ይህን መግለጫ ለማውጣት እንደፈለገ ግልጽ ባያድረግም ስምምነቱን የመጣስ ሙከራ ስለመኖሩ አመልካች እንደሆነ ከግምት በላይ አስተያየት እየተሰጠ ነው። መንግስት መመሪያውን በጣሱ አካላት ላይ እርምጃ ከውሰደ ለጣልቃ ገብነት መነሻ ምክንያት ለማድረግ ታስቦ እንደሆንም ተመልክቷል።
It is to be recalled that as of June 30th 2021, a NOTAM& AIP SUP has been issued with reference number (A0166/21 and AIP SUP A 04 2021) by the Ethiopian Civil Aviation Authority. Therefore, violations against the above NOTAM will result in high risk to any operators and/or pilots. Entities violating the issued NOTAM therefore assumes full responsibility for any related actions.
- የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ“ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ” እያሉ በስሟ ሲምሉ የነበሩ ብዙዎች ነበሩ፤ ከልባቸው ለቃላቸው ታምነው ልጅ የሆኗት ግን ጥቂቶች ብቻ ናቸው። አንዳንዶች በስሟ የሚገዘቱት እንጀራዋን ለመብላት እንጂ መከራዋን ለመካፈል አይደለም፤… Read more: የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ
- አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ“ወገኖቼ እንማርና እናስተምር፣ ወንጀልን እንጸየፈው፣ እንጥላው፣ ወንጀልን ተጸይፈን ወንጌልን እንውደደው፣ በወንጌል እንኑር፣ ወንጌል ሕጓም ስርዓቷም ያማረች ናት፤ ወንጌላዊ መኾን መልካም ነው፣ ወንጀለኛ መኾን ግን ሐጥያት ነው… Read more: አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ
- ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናውቤት የተባለች አንዲት ሴት እንዲህ ብላለች፦ “ደም ማነስ የያዘኝ በአሥራዎቹ ዕድሜ ሳለሁ ነው። ቶሎ ይደክመኝ፣ አጥንቶቼን ይቆረጥመኝ፣ እንዲሁም ትኩረቴ በቀላሉ ይከፋፈል ነበር። ሐኪሜ የብረት ማዕድን አዘዘልኝ።… Read more: ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናው
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ ወገኖች አስታውቀዋል። ጎን ለጎን የትግራይ ከፍተኛ ባለስልጣናትና የዞን አስተዳዳሪዎች የተባሉ… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ። ለውጭ አገር ሚዲያዎች ዜና የሚያቀብሉና እነሱኑ የሚከተሉ ስምምነቱ መክሸፉንና መንግስት… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት