ለሜቻ ግርማ ” ካሁን በሁዋላ ዋጋ የለውም፤ መወዳደር አይችልም” በሚል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽ የህክምና ባለሙያና ቴክኒክ ክፍሉ ያሟርተበትና ያባረረው አትሌት ነው። ፌዴሬሽኑ በቅርቡ በሰጠው መግለጫ “ህዝባችን ይወቅልን” ሲሉ ካነሳቸው ጉድዮች አንዱ የለሜቻ ወደ ኦሊምፒክ መጓዝን ነበር። ዛሬ ከቶኪዮ የሚወጡ ሪፖርቶች እንደሚሉት አትሌቱ የርቀቱ ኮከቦች ለሆኑት ኪንያውያን ስጋት እንደሆነ ተደርጎ ነው።
የለሜቻን ጉዳይ አንስተን በዛው አክሉ ባለሙያዎች የሰማነውን ምስክረነት መዘገባችን ይታወሳል። ለሜቻ አትሊቲክስ ፌዴሬሽን ” ዋጋ የለህም ” በሚል ባባረረው ሳምንት ጊዜ ውስጥ ሞናኮ ዳይመንድ ሊግ ተሳትፎ 8፡07 በመሮጥ ሪከርድ አስመዝግቦ ቢያሸንፍም ፌዴሬሽኑ ” ሞቼ እገኛለሁ” ብሎ አቋሙን እንደማይቀይር አስታወቀ። ባደርግነው ማጣራት የለሜቻ አሰልጣኝ አሁን የብሄራዊ ቡድኑ የ3000 ሜትር መሰናክል ኮች ነው ” እባካችሁን ይህን ልጅ እድል ስጡት” ቢልም ሊሰሙት አልቻሉም።
በመጨረሻ እነ አሃይሌ ገብረስላሴ ያሉበት የኦሊምፒክ ኮሚቴ የቴክኒክ ቡድን ከባለሙያዎች ጋር መክሮ ለሜቻን አስመዘገበና ቶኪዮ ወሰደ። በዛሬው ምሽት እንደታየው ለሜቻ ሜዳሊያ ውስጥ እንደሚገባ ሰፊ ግምት ያገኝበትን ውድድር አድርጎ ለቀታዩ ፉክክር አልፏል። ባልደረባው ጌትነት ዋለም በጥሩ ብቃት ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፉን ተከትሎ ሁለቱም ኪንያዊያኖቹን እንደሚፈትኑ እየተነገረላቸው ነው።
ማምሻውን በተካሄደው ማጣሪይ ምድብ አንድን አትሌት ለሜቻ ግርማ በአንደኝነት ሲያተናቅቅ፣በምድብ ሁለት የተወዳደረው አትሌት ጌትነት ዋለ ሁለተኛ ሆኖ ጨርሷል። ከውድድሩ በሁዋላ ለሜቻ ግርማ ከፍ ያለ ግምት የተሰጠው አትሌት ሆኗል።
ተክለ ሰውነቱ፣ ልጅነቱና ጉልበቱ ከ3000 መሰናክል ብቁ ተወዳዳሪ እንደሚያደርገው ተነግሮት በዛው የቀጠለው ለሜቻ በ3ሺህ ሜትር የኢትዮጵያ ክብረወሰን ባለቤት እንደሆነ መረጃዎች ያመልክታሉ።
ከውድድሩ በሁዋላ ኢዜአ “አትሌቱ እአአ 2019 ኳታር ዶሃ በተከናወነው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁ ይታወሳል::አትሌት ጌትነት ዋለ በበኩሉ በዚህ ውድድር ትልቁ ውጤቱ እአአ 2016 በተካሄደ የዓለም ከ20 አመት በታች ውድድር ሶስተኛ በመውጣት የነሃስ ሜዳሊያ ያሸነፈበት ነው። ኬንያ እአአ ከ1984 ጀምሮ በዘጠኝ ተከታታይ ኦሊምፒክ መደረኮች የወርቅ ሜዳሊያዎችን በማሸነፍ የበላይነቱን ይዛለች::በዚህም 3 ሺህ ሜትር መሰናክል የኬንያ የባህል ስፖርት ተብሎ እስከመጠራት ደርሷል” ሲል ቅድመ ውጤታቸው ጽፎላቸዋል።
በዘንድሮው የቶክዮ 2020 ውድድር ግን ኬንያውንያኑ አትሌቶች በተለይም ከኢትዮጵያ እና ከሞሮኮ አትሌቶች ጠንካራ ፉክክር እንደሚጠብቃቸው ተነግሯል::የአፍሪካ ተወካዮቹ ኢትዮጵያ ፤ኬንያ እና ሞኮሮ በፍጻሜው ውድድር ላይ በሁለት ሁለት አትሌቶች የተወከሉ ሀገራት ናቸው።የ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ውድድሩ ሰኞ ሐምሌ 26 -2013 ከቀኑ በ9:15 ይካሄዳል።
- ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናውቤት የተባለች አንዲት ሴት እንዲህ ብላለች፦ “ደም ማነስ የያዘኝ በአሥራዎቹ ዕድሜ ሳለሁ ነው። ቶሎ ይደክመኝ፣ አጥንቶቼን ይቆረጥመኝ፣ እንዲሁም ትኩረቴ በቀላሉ ይከፋፈል ነበር።… Read more: ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናው
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ ወገኖች አስታውቀዋል። ጎን ለጎን የትግራይ ከፍተኛ… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ። ለውጭ አገር ሚዲያዎች ዜና የሚያቀብሉና እነሱኑ… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት
- የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡምየፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የትራንስፖርት ስምሪትና የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር ሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ 11 ግለሰቦች በስር ፍ/ቤት የተሰጠውን ዋስትና አፀና። ፍርድ ቤቱ ተጠርጣሪዎቹ… Read more: የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡም
- መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለየአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ ምክንያቱም “የኢትዮጵያ መንግሥት በሕገ ወጥ መንገድ የአውሮፓ ኅብረት አገራት ውስጥ የሚኖሩ ዜጎቹን መልሶ ለመቀበል… Read more: መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ