“ፓርቲዎቹ ” ይላል ኔድ ፕሪስ ሲጀመር። መንግስትንና “አሸባሪ” ተብሎ የተሰየመውን ትህነግን ማታቸው ነው። ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ፣ በአፋጣኝ፣ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ተኩስ እንዲያቆሙና ሁሉን አቀፍ ወደሆነ የፖለቲካ ንግግር እንዲያደርጉ ያሳስባል። ሁለቱም የንግግሩን ዓላማ የሚያስት ምልልስ እንዲቆጠቡ ያሳባል።
ላለፉት 50 አመታት በትህነግ አማካይነት መሰቃየታቸውን፣ በረሃ እያለ፣ መንግስት ሆኖ፣ ከመንግስትነት ከተወገደ በሁውላ ሽብርን በየክልሉ እየፈለፈለና የልዩነት ፖለቲካን እያዘራ ሰላም የነሳው ትህንግ ለመጨረሻ ጊዜ ከኢትዮጵያ ፖለቲካ ታሪክ እንዲፋቅ ዘመቻ ክተት መታወጁ አይዘነጋም።
በሚሊዮኖች ከዳር እስከዳር ንቅናቄ ፈጥረው የአገር መከላከያን ለመቀላቀል ጥያቄ አቅርበውና፣ ሌሎችም በወዶ ዘማችነትና በክተት ወደ ግዳጅ እያመሩ ባሉበት ወቅት አሜሪካ ይህን አስገዳጅ መግለጫ ማውጣቷ አስገራሚ ሆኗል።
በቲውተር መልዕክቱ ስር ” አፋራና አማራ ክልል ሲወጋ የት ነበራችሁ?” ከሚለው ምጸት ጀምሮ አሜሪካኖችን ” አሁን ትህነግ ዙሪያው ተከቦ መደቆስ ሲጀምር ተኩስ አቁም የምትሉ … በሚል ክፉኛ ዘለፋ ተገጥግጧል።
ከትናንት በስቲያ ጌታቸው ረዳ ለመደራደር ዝግጁ መሆኑንን አስታውቆ፣ ትናንት ደግሞ ትህነግ ከቀድሞው ስምንት ቅድመ ሁኔታዎች ተቀንሶ በስድት ቅድመ ሁኔታዎች የተጀበ የሰላማዊ የንግግር መግለጫ አሰራጭቶ ነበር።
በጀት፣ አገልግሎት፣ ነጻ ትራንስፖርት፣ የመሳሰሉት ባስቸኳይ እንዲፈቀዱለት ትህነግ መጠየቁን ተከትሎ ” አንድ በሽብርተኛ ቡድን የምትወጋ አገር ለሚወጋት ድርጅት እንዴት በጀትና አገልግሎት ታቀርባለች?” የሚል የመርህ ጥያቄ ለአቶ ጌታቸው ቀርቦ ነበር።
አዲስ አበባ ለመግባት መንገድ ሲያማርጡ የነበሩት ትህነጎች በምን ዓይነት ተዓምር በዚህ ሶስት ቀናት ውስጥ የሰላማዊ ድርድር ሃሳብ ለማቀንቀን እንደተነሱ በግልጽ ባይነገርም፣ በጅቡቲ መስመር መንገድ ዘግቶና፣ በወልደያ በኩል እስከ ደሴ በመዝለቅ የመደራደሪያ ሃይላቸውን ለመጨመር ያደረጉት ጥረት በኪሳራ ስለከሸፈ እንደሆነ ግምት አለ።
በተለይም በአፋር ግንባር ሶስት ክፍለጦር የተደመሰሰበት ትህነግ፣ የኪሳራው መጠን በመከላከያና በአፋር ልዩ ሃይል ይፋ ከሆነ በሁዋላ፣ በማይጸብሪ የሱዳንን ኮሪዶር ለማስከፈት በተደጋጋሚ ያደረገው ሙከራ እጅግ ሰፊ ዋጋ አስከፍሎት ባለመሳካቱ እርቅን አማራጩ ለማድረግ እንዲገደድ እንዳደረገው ዜናውን ተከትሎ መረጃ እየወጣ ነው።
አቃቤ ህግ አሁን በህይወት ባሉት አመራሮች ላይ ሰፊ መረጃ አዘጋጅቶ ክስ ከመጀመሩና የክስ ሂደቱን እያጣደፈ ባለበት ውቅት አሜሪካ አስቸኳይ የተኩስ አቁም እንዲደረግ መጠየቋ “ድርድር እንዴት” የሚል ጥያቄ አስነስቷል።
ትህነግ የማጥቃት ሂደት ላይ በነበረበት ወቅት ማርቲን ፕላውት የሚባለው የትህነግ ተከፋይ የህዝብ ግንኙነት፣ ዶ/ር ደብረጽዮንን እንደነገሩት ተቅሶ “ትህነግ የጅቡቲን መስመር ተቆጥጥሮ እርዳታውን በቀጥታ ወደ ጅቡቲ ያስገባል” በሚልበት ወቅትና እነ ጌታቸው ወደ ደብረብረሃን፣ አዲስ አበባ፣ ወልቃይት ጎንደር … አራት ኪሎ እያሉ መነገድ ሲያማርጡ አሜሪካ ጸጥ ብላ እንደነበር ይታወሳል። ከሁሉም በላይ ዓለም በሚከለክለው ሕጻናትን በጦርነት የመማገድ ወንጀል ትህነግ በሚታክት ማስረጃ ሲከሰስ አሁንም አሜሪካ ተለጉማ ነበር።
የአሜሪካንን ጥሪ አስመልክቶ ከትህነግ በኩል ይቃወማሉ የሚል ግምት ባይኖርም ይህ እስከተሳፈ ድረስ በይፋ የተባለ ነገር የለም።
ይህ መግለጫ ከመውታቱ በፊት የ ሳማታን ፓወር መንግስት ለማሰገደድና ለመጫን በዛሬው ዕለት ወደ አዲስ አበባ እንደሚመጡ በይፋ ተገልጾ ነበር። ሴትየዋ ጥሩ የሚባሉ የትህነግ ወዳጅ እንደሆኑ የሚነገርላቸው ናቸው።
- የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ“ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ” እያሉ በስሟ ሲምሉ የነበሩ ብዙዎች ነበሩ፤ ከልባቸው ለቃላቸው ታምነው ልጅ የሆኗት ግን ጥቂቶች ብቻ ናቸው። አንዳንዶች በስሟ የሚገዘቱት እንጀራዋን… Read more: የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ
- አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ“ወገኖቼ እንማርና እናስተምር፣ ወንጀልን እንጸየፈው፣ እንጥላው፣ ወንጀልን ተጸይፈን ወንጌልን እንውደደው፣ በወንጌል እንኑር፣ ወንጌል ሕጓም ስርዓቷም ያማረች ናት፤ ወንጌላዊ መኾን መልካም ነው፣… Read more: አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ
- ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናውቤት የተባለች አንዲት ሴት እንዲህ ብላለች፦ “ደም ማነስ የያዘኝ በአሥራዎቹ ዕድሜ ሳለሁ ነው። ቶሎ ይደክመኝ፣ አጥንቶቼን ይቆረጥመኝ፣ እንዲሁም ትኩረቴ በቀላሉ ይከፋፈል… Read more: ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናው
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ ወገኖች አስታውቀዋል። ጎን ለጎን የትግራይ… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ። ለውጭ አገር ሚዲያዎች ዜና የሚያቀብሉና… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት