ETHIO12.COM

“ የሪፐብሊኩ ጥበቃ ሃይል ሰሜን በመርሳ ድሬ ሮቃ ጁንታውን ድባቅ መታ”

ነሀሴ 29 ቀን 2013

ታታሪውና አይደፈሬው የሪፐብሊኩ ጥበቃ ሃይል በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን በመርሳ ድሬ ሮቃ በሚባል አከባቢ ጁንታውን ድባቅ መታው ።

በአፋር ክልል ሚሌ መስመርን ለመያዝ ቋምጦ በሰሜን ወሎ ዞን መርሳ ወረዳ ድሬ ሮቃ በተባለ አካባቢ በአራት አቅጣጫ ማለትም በጮቤ፡በቀለንቲ:ሰርጢ እና ቀላ በተባሉ ተራሮችን ለመያዝ እና ሰብሮ ለመግባት የመጣውን አሸባሪ ሃይል ይዞት ከመጣው ሰውና ማቴርያል ጋር መደምሰሱን የሪፐብሊኩ ጥበቃ ሃይል የአንድ ብርጌድ ዋና አዛዥ ተናገሩ ።

የሪፐብሊኩ ጥበቃ ሃይል ከአጋር ክፍሎች ጋር በመሆን ሽብርተኛው ያደረጋቸው ተደጋጋሚ ሙከራዎችን በማክሸፍ አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቷል ብለዋል ።

በዚህም 431 ተደምስሷል ። 60 ክላሽ ፣ ብሬን 3 ፣ ስናይፐር 2 እና 1 መገናኛ ሬዲዮ ተማርኳል ።

በተለይ የአከባቢው ማህበረሰብ እና ታጣቂ ሰላሙን ነቅቶ ከማስጠበቅ ጎን ለጎን ሰራዊቱ በተሳካ ሁኔታ በግዳጁ ድል እንዲያመጣ ትልቅ እገዛ ያደረገ ሲሆን ፣ በዚህም ምግብ ፣ ውሃ ፣ ተተኳሽ ሰራዊቱ እስካለበት ድርስ በማቅረብ እና አብሮነቱን በማጠናከር ለተገኘው ድል የአንበሳውን ድርሻ መያዙን የአንድ ብርጌድ ም/አዛዥ ተናግረዋል ፡፡

የቀበሌ 24 ሊቀመንበር አቶ ሃሰን ከረሙ መሃመድ ፣ ህዝቡን ፣ ወጣቱንና ታጣቂውን በማደራጀት አከባቢያችንን እየጠበቅን ሲሆን ፣ ጁንታው ወደ አካባቢያችን በተደጋጋሚ ሊገባ ሙከራዎችን ያደረገ ቢሆንም ጠንክረን በመመከት ቀበሌያችንን ሳናስደፍር ቆይተናል ። ሰራዊታችን ከመጣ በኋላም ሁሉም የቀበሌያችን ነዋሪ እስከ ግንባር ድረስ በመዝለቅ ስንቅ ፣ ተተኳሽ ለጀግናው ሰራዊታችን እያቀረብን እንገኛለን በተገኘው ድልም ኮርተንበታል በማለት ተናግረዋል፡፡

ደመላሽ ጥላሁን (ከግዳጅ ቀጣና)
ፎቶግራፍ ምትኩ ገብሩ እና መዝገቡ ያረጋል

Exit mobile version