Site icon ETHIO12.COM

በሰሜን ወሎ በኩል ሰርጎ የገባው አሸባሪ በጀግናው መከላከያ ሰራዊታችን እርምጃ ተወሰደበት

ነሀሴ 29 ቀን 2013

በሰሜን ወሎ በኩል ሰርጎ የገባው ወራሪው የህውሃት አሸባሪ ሃይል በጀግናው መከላከያ ሰራዊታችን አፀፋዊ እርምጃ ተወሰደበት ፡፡

በዚህ ስምሪት 142 የሽብር ቡድኑ ታጣቂ ሃይል ሲደመሰስ 4 ስናይፕር ፣ 6 የሞርተር ቅንቡላ ፣ 1 ብሬን ፣18 የእጅ ቦምብ ፣ 15 ክላሽ ፣ 7 ሽህ የብሬን ጥይት ፣ 5 ሽህ የክላሽ ጥይት ፣ 1 የመገናኛ ሬዲዬ (1187 አይኮም) ፣ 1 የዋይፋይ ሪሲቨር ፣ 6 የብሬን ሻንጣና 10 የነፍስ ወከፍ ወታደራዊ የወገብ ሻንጣ ከጠላት ሃይል ተማርኳል ።

ከግንባሩ አመራሮች መካከል የክ/ጦር ም/አዛዥ ለኦፕሬሽናል እንደተናገሩት ፣ ጠላት አሁን ላይ በሰራዊታችን እየደረሰበት ባለው ኪሳራና ባጋጠመው ሽንፈት የተስፋ መቁረጥ እንቅስቃሴዎችን ቢያደርግም ከገባበት መግደያ ወረዳ መውጣት እንደማይቻለው ገልፀው ፤ ወራሪውን ሃይል በገባበት አስቀርተን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለህዝባችን የድል ዜና እናሰማለን ብለዋል ።

በግዳጅ ቀጣናው የብርጌድ ዋና አዛዥ በበኩላቸው ፣ በጭፍን ሃገራዊ ጥላቻ ተነሳስቶ የማይሞከረውን መከላከያ ሰራዊት በመፃረር ህዝብን የተዳፈረው አሸባሪ የትህነግ ቡድን በፈፀመው ስህተት የእጁን እያገኘ ነው ሲሉ ተናግረዋል ።

ሰራዊታችን በተሰለፈበት የወሎ ግንባር በሰርጎ ገቡ ሽብርተኛ ቡድን ላይ እየወሰደ ያለው አሁናዊ እርምጃና በጠላት በኩል የተመለከትነው መፍረክረክ የፍፃሜውን መቃረብ የሚያመላክት ነው ያሉት ደግሞ በግንባሩ የብርጌድ ም/አዛዥ ለኦፕሬሽናል ናቸው።

ኤፍሬም አድማሱ
ፎቶግራፍ ታጠቅ ንጉሴ

Exit mobile version