Site icon ETHIO12.COM

ዩክሬን ከአየር የሚመጣ ጥቃት መከላከል አትችልም ” አብቅቶለታል”፤ ፕሬዚዳንቱ ደም እንዲለገስ ጠየቁ፤

“ዓለም ሁሉ ከዩከሬን ጋር በጸሎት አብሮ ነው” ሲሉ ጆ ባይደን ሰማያዊ መፍትሄ የተመኙለት የዩክሬን ቀውስ ወደ ጦረነት ሲቀየር ቅድሚያ የተደረገው የዩክሬንን የአየር ጥቃት መከላከል አቅም አልባ ማድረግ ነበር። የፎክስ ቲቪ ወኮል ከኬቭ በቀጥታ ” It has gone” ሲል የዩክሬን የአየር መከላከያ ሙሉ በሙሉ በውደሙን ዘግቧል።

ፐሬዚዳንት ጆ ባይደን የተከተሉትን መንገድ ሲተች የሰነበተውና ” ትራምፕ በስልጣን ላይ ቢሆኑ ኖሮ ይህ አይሆንም ነበር” የሚል ጠንካራ ወቀሳ ያተመው የፎክስ ቲቪ ዘጋቢ ስቲቭ ከኬቭ እንዳለው የዩክሬን የአየር መከላከያ አቅም አልባ መሆኑንንብቻ ሳይሆን፣ የሩሲያ ሃይሎች ወደ በተለያዩ አቅጣጫዎች ወደ ዋና ከተማዋ እያመሩ መሆኑንን ነው።

በዩክሬን 40 ሰዎች መሞታቸውና ከዛም ውስጥ 10 ሲቪል እንደሆኑ፣ ቁጥሩም ከዛ በላይ እንደሚጨምር መረጃዎች ከኬቭ እየወጡ ነው። የዩክሬን ፕሬዚዳንት ደም እንዲለገስ ጠይቀዋል። ውቀታዊ ሁኔታዎችን ለማሳወቅ በአገራቸው ቴሌቪዥን የቀረቡት ፐሬዚዳንቱ፣ በአገሪቱ የክተት አዋጅ ጥሪም አስተላልፈዋል።

ኔቶ አንድን ሰላማዊ አገር፣ ሉዓላዊ አገር፣ መውረር ተቀባይነት እንደሌለው በዋና ጸሃፊው ስቶልተንበርግ አማካይነት ዛሬ ረፋዱ ላይ አስታውቋል። ኔቶ በባህር፣ በየብስና በአየር ያሰማራውን ሃይል ይፋ አድርጓል። ዋና ጸሃፊው ” የተሰባሰብነበት ዋና ዓላማ ይህ ነው” ሲሉ ሩሲያ አሁን እየፈጸመች ላለው ተግባሯ የጋራ ምላሽ እንደሚሰጥ፣ ሰላምም ዋጋ እንደሚያስከፍል፣ አውሮፓ ከስጋት ነጻ መሆን እንዳለበት ገልጸዋል።

ናቶ ጀቶች በዝግጅት ላይ መሆናቸውንና ወታደራዊ እቅዳቸውን በየትኛውም ጊዜ ሊያከናውኑ እንደሚችሉም ዋና ጸሃፊው አስታውቀዋል። ዝርዝሩን ግን ለጊዜው ይፋ እንደማያደርጉ ተናግረዋል። እንደ ጸሃፊው ገለጻ ኔቶ ያመረረ መሆኑ ተመልክቷል። ነገ የኔቶ አገሮች ይሰበሰባሉ።

ቢቢሲ የሚከተሉትን ማስታወሻዎች ለመረጃ እንዲሆኑ በገጹ አስፍሯል።

Exit mobile version