Site icon ETHIO12.COM

ዓለም ባንክ 58 ሚሊዮን ዕርዳታ፣ 107 ሚሊዮን ብድር ሰጠ

የመሬት መራቆትን በመቀንስ ምርታማነትን ለመጨመር የሚውል የ165 ነጥብ 2 ሚሊየን ዶላር የእርዳታና የብድር ስምምነት መፈረሙ ተገለጸ። ትህነግ ከተሸነፈና የኢትዮጵያ የመከላከያ አቅም ከተነከረ በሁዋላ የላላውን ተጽዕኖ ተከትሎ የዓለም ባንክ በተከታታይ ዕርድታ እየለቀቀ ነው።

ይህ በኢትዮጵያ መንግሥትና በዓለም ባንክ መካከል መካከል የተደረገው ስምምነት በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ 170 ወረዳዎችና በ217 ተፋሰሶች ተግባራዊ የሚደረግ ሲሆን፣ የተፈጥሮ ሀብት ልምዶችን  በማስፋፋት በ789ሺህ ቤተሰቦች ውስጥ የታቀፉ 4 ሚሊየን ወገኖችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ዝርዝር መረሃ ግብር እንዳለው የመንግስት መገናኛዎች ተቋማቱን ጠቅሰው አመልክተዋል።

ከዚህም በተጨማሪም የተሰጠው ድጋፍ በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ ለድርቅ ተጋላጭ የሆኑና ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን አርሶ አደሮችን ኑሮ ለማሻሻል የሚውል እንደሆነ ተመልክቷል።

በግሪን ክላይሜት ፈንድ (GCF) ከተገኘውና በአለም ባንክ በኩል ተግባራዊ ከተደረገው በጀት ውስጥ 58 ሚሊየን ዶላሩ በዕርዳታ መልኩ የተሰጠ ሲሆን÷ 107 ሚሊየን ዶላሩ ደግሞ በረጅም ጊዜ የሚከፈል  ብድር መሆኑ ታውቋል፡፡

የገንዘብ ድጋፍ ስምምነቱን በገንዘብ ሚኒስቴር የኢኮኖሚ ትብብር ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው እና በአለም ባንክን  የግሪን ክላይሜት ፈንድ ተወካይ አቶ አሳዬ ለገሰ መፈረሙን ከገንዘብ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡

Exit mobile version