Site icon ETHIO12.COM

ጦርነት ምን እንደሚያስከፍል አይተነዋል ፣ የሰላምን ዋጋ ግን አልተገነዘብንም!

ቁጥር እንስጥ ከተባለ ትናንትም ፣ ዛሬም፣ ነገም የአማራም የኢትዮጵያም አንደኛ ጠላት ህወሓት ነው። ህወሓት ማለት ለአንድ ሺህ ዘመን በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ከማልቀስና ከማፍረስ የዘለለ አዎንታዊ አስተዋፅኦ የሌለው ፣ በየዘመኑ እያገረሸ ሀገር የሚያደማ አውራጃዊ ልሂቅ መንፈስ ነው። ህወሓት የዝርፊያና የደም ማፍሰስ ምሱን ትቶ ፣ ከዳርቻ ፖለቲካ ወጥቶ በሰላም ለመኖር ተፈጥሮው አይፈቅድለትም። በመጀመሪያ ደረጃ ይህን ኃይል ከትግራይ ህዝብና ከትግራይ እጣፋንታ ለመነጠል ድፍረትና ብልሃት የሌለው መፍትሔ ፋይዳ ቢስ ነው።
  1. የሀገራችን ጉዳይ ከእለት እለት ይበልጥ የማይጨበጥና አስጊ እየሆነ ነው። የትግራይ ወራሪ ኃይል የለኮሰው ጦርነት በምን እንደሚቋጭ አይታወቅም። በአንድ ወገን ህወሓት ለጦርነት እየተዘጋጀ ፣ ኦነግ/ሸኔና ሌሎች የአመፅ ኃይሎች ይበልጥ እየተጠናከሩ ነው። በሌላ ወገን አማራው ከወረራው ጉዳት እንዳያገግም ፣ ለደህንነት ስጋቱ መፍትሔ እንዳይፈልግ ውስጣዊ ሰላም እያጣ ነው። በዚህ ሁሉ ትርምስ ላይ የሰላምና ድርድር ወሬ ይናፈሳል ፤ የሀገራዊ ምክክርና ውይይት ይደገሳል።
  2. ዘላቂ መፍትሔ ከፈለግን ከማይጥሙ ጥያቄዎች ጋር መጋፈጥ አለብን። የጦርነትን አስከፊነት አይተናል ፣ ለሰላምስ የምንከፍለው ዋጋ ምን ያህል ነው? ስለሰላም የምንመክረውና የምንደራደረው ከማን ጋር ነው ? በማን ኪሳራ ፣ በምን ስሌት ነው ሰላም የሚመጣው ?በተለይ ህወሓት የሰላም ዋጋ የሚገባው ፣ ለሰላማዊ ድርድር ክብር ሊሰጠው የሚገባ ኃይል ነው ወይ ? ከእንግዲህ ትግራይና የትግራይ ህዝብ ከአማራም ሆነ ከኢትዮጵያ ጋር የሚኖራቸው እጣፋንታ ምን ሊሆን ይችላል?
  3. ቁጥር እንስጥ ከተባለ ትናንትም ፣ ዛሬም፣ ነገም የአማራም የኢትዮጵያም አንደኛ ጠላት ህወሓት ነው። ህወሓት ማለት ለአንድ ሺህ ዘመን በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ከማልቀስና ከማፍረስ የዘለለ አዎንታዊ አስተዋፅኦ የሌለው ፣ በየዘመኑ እያገረሸ ሀገር የሚያደማ አውራጃዊ ልሂቅ መንፈስ ነው። ህወሓት የዝርፊያና የደም ማፍሰስ ምሱን ትቶ ፣ ከዳርቻ ፖለቲካ ወጥቶ በሰላም ለመኖር ተፈጥሮው አይፈቅድለትም። በመጀመሪያ ደረጃ ይህን ኃይል ከትግራይ ህዝብና ከትግራይ እጣፋንታ ለመነጠል ድፍረትና ብልሃት የሌለው መፍትሔ ፋይዳ ቢስ ነው።
  4. የዋህ አንሁን። ከታሪክ አንፃር የአንድ ሚሊኒየም ጣረሞት የተጫነውን የአማራና የትግራይን ህዝብ “ወንድማማችነት” እንደተማላ መልሶ ነፍስ መዝራት ጉም እንደ መዝገን ዓይነት ነው። ከቶንስ የአማራ ህዝብ ከአጋም ጉርብትና የተረፈው ከውጋት ፣ ከሸክምና አመድ አፋሽነት ሌላ ምንድነው ? የትግራይ ህዝብ ከተጣወረው የህወሓት መንፈስ ፍፁም ካልተላቀቀ በቀር የአማራም የሌላውም ህዝብ ወዳጅ ይሆናል ማለት ዘበት ነው። ያለፉት 40 ዓመታትን ቁስል ለማሻር እንኳን ገና በርካታ በጎ ትውልዶችን ይጠይቃል።
  5. ካነሳነው አይቀር “ጦርነቱ የአማራ አይደለም ” ፣ “ወያኔን አሳልፈን ከኦህዴድ – ብልፅግና እንገላገል” የሚሉት ሃሳቦች የደደቦች ፣ የክፉዎችና የሰነፎች ናቸው። ደደቦች ስለማይሰሙ እንዝለላቸው። ክፉዎች የአማራን ህዝብ በጠላትነት መርዘው ለማዳከምና ለማጥፋት የማይተኙ አዛኝ ቅቤ አንጓቾች ናቸው። ከአማራው በላይ አማራ መስለው ግፍና በደል ይዘረዝራሉ ፣ ሬሳ ይቆጥራሉ። “ህወሓትስ ከዚህ በላይ ምን በደለህ ?” እያሉ አማራ ጠላቴ ነው ብሎ የተነሳ ብቸኛ ድርጅትና ለአርባ ዓመታት በግልፅ ሲያደማው የነበረ መሆኑን ፣ ህወሓት የኦህዴድም ፣ የብአዴንም ፣ የብልፅግናም ፈጣሪነቱን ለመሸፈን ይባጃሉ። ሾርት ሚሞሪ አይደለንም!
  6. ሰነፎች ያው ገልቱዎች ናቸው። ከ1983 ታሪክ የመማር እንኳን ወኔ የላቸውም። ትግልና መስዋዕትነት ፣ ላብና ደም መክፈል አይፈልጉም። እነሱ በሚዲያ ፈረስ ተፈናጥጠው ፣ ምናባዊ ግንባር ከፍተው ያዘው ፣ ፍለጠው ቁረጠው ሲሉ ይውላሉ። አፈር ሳይነካቸው ህወሓት ቆስሎ ደምቶና እንደ አንበጣ ሞቶ ሥልጣን በወርቅ ሳህን እንዲሰጣቸው ይፈልጋሉ። ወንድሜ ! ብልፅግና በድሎኛል ፣ አብይ አንገሽግሾኛል ካልክ ወገብህን ጠበቅ ፣ ሀሞትህን ዋጥ አድርገህ መታገል እንጂ በወያኔ ጀርባ ታዝዬ ልሞሸር ማለት አፀያፊ ነው።
  7. ጦርነት የሰውን ልጅ አውሬ የሚያደርግ እጅግ አስከፊ ድርጊት ነው። በገዛ ቤታችን አይተነዋል። ነገር ግን ሰላም በአንድ ወገን ምኞትም ሆነ ፀሎት ፣ ኪሳራና ተንበርካኪነት አይመጣም። አንድ ሺህ ጊዜ ተፈትኖ ያላዋጣ መፍትሔ በመድገም አይገኝም። ሰላም ለማግኘት ጠንክሮ መስራትና ለጦርነትም መዘጋጀት የግድ ነው። አስቸጋሪ ውሳኔዎችን በጥበብና በአስተዋይነት መውሰድ ፣ የሩቢከንን ወንዝ በቆራጥነት መሻገር ያስፈልጋል። ነቀርሳውን ህወሓትን ቆርጦ መጣል ለኢትዮጵያም ፣ ለአማራም ፣ በአጠቃላይ ለአፍሪካ ቀንድም ዘላቂ ሰላም የማይታለፍ ቅድመ ሁኔታ ነው። ለትግራይም ህዝብ ታላቅ ውለታ ነው።

ይህ ጽሁፍ በጁን 11,2022 የተጻፈ ነው ። ጸሐፊው Dr. Tewodros Hailemariam ናቸው። ጠቃሚ መልዕክት አለው በማለት አቶ ውብሸት በቴሌግራም ገጻቸው ካካፈሉት እንዳገኙት ጠቅሰው አንባቢ የሆኑ ልከውልን አትመነዋል። አቋሙም ሆነ አሳቡ የጸሃፊው ነው።

Exit mobile version