Site icon ETHIO12.COM

አጀኢባ ጥንከሬዋ አጃኢብ ነው‼

የአካል ጉዳት ያልበገራት ተማሪ አጃኢባ ያሲን ሽኩር የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን በእግሯ በመሥራት አርአያ ሆናለች።

የአካል ጉዳተኝነት ትምህርትን ጨምሮ ከማንኛውም ማኅበራዊ መስተጋብር እንደማያግድ ተማሪ አጃኢባን ማየት በቂ ነው።

ተነሳሽነት ካለ አካል ጉዳተኝነት አላማን ከማሳካት እንደማያግድ በአዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን በእግሯ እየሰራች ያለችው ተማሪ አጃኢባ ጥሩ ማሳያም ጭምር ሆናለች።

የተማሪዋ ፈተናውን በእግሯ መሥራት አካል ጉዳተኝነት ተሰጥኦንና ተነሳሽነትን ከግብ ከማድረስ እንደማያግድም አመላካች ነው።

ተማሪ አጀኢባ አካል ጉዳተኝነት ግብን ለማሳካት ከመጣር እንደማያግድ ለበርካቶች ማስተማሪያም ጭምር መሆኗን ኢዜአ ዘግቧል።

Exit mobile version