“ዐጼ ምኒልክ የጦር ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት ያቋቋሙበት ቀን የሀገር መከላከያ ሠራዊት ቀን ኾኖ እንዲከበር ተደርጓል” ሲሉ በዓሉ 119 ዓመታትን ወደሁዋላ ሄዶ በዓሉን ማክበር የተፈለገበትን ምክንያት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ አስታወቁ።
የኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በ116ኛ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ቀን አከባበር ላይ ንግግር ነው ይህን ያሉት። ፊልድ ማርሻሉ ኢትዮጵያ ረጅም ዕድሜ ያላት ቀደምት እና በትውልድ ቅብብሎሽ የዘለቀች ታላቅ ሀገር መኾኗን ገልጸዋል።
በእነዚህ ረጅም የታሪክ ዘመናትም በየትውልዱ በነበሩ ልጆቿ ተጋድሎ ነጻነቷ እና ክብሯ ተጠብቆ የተላለፈችልን ሀገር ናት ብለዋል።
መንግሥት በተለወጠ ቁጥር የሀገር እሴቶች እየፈረሱ በመሄዳቸው ቀደምት ጀግኖች እና ባለድሎች እየተዘነጉ፣ ተተኪው ትውልድም የጀግንነት እና የአርበኝነት ሞዴል እንዳያገኝ የሚያደርጉ ፖለቲካዊ እሳቤዎች ሲያጋጥሙን ቆይተዋል ነው ያሉት።
በተለያዩ ጊዜያት ወደ ሥልጣን በመጡ መሪዎች እሳቤ ላይ ብቻ ተመስርተው ሲጻፉ የነበሩ ታሪኮች የጭቅጭቅ እና የግጭት መንስዔ ስለመኾናቸውም ተናግረዋል።
ትውልድ በጋራ የተግባባበት የጋራ ታሪክ ባለመኖሩ በአንድነት ቆሞ ሀገሩን ከመገንባት ይልቅ ገዥዎች በሚሰጡት አጀንዳ ጎራ ለይቶ ለመናቆር ተገዷል ብለዋል።
ለአብነትም በፊት ይከበር የነበረው የሀገር መከላከያ ሠራዊት ቀን የቀደምት ጀግኖችን ታሪክ ቆርጦ ያስቀረ እና የረሳ ነበር ነው ያሉት። ከለውጡ በኋላ በተደረሰው ውሳኔ መሠረት ቀኑ ታሪክን አካታች በኾነ መልኩ እንዲከበር ኾኗል ነው ያሉት ፊልድ ማርሻሉ።
የመከላከያ ሠራዊት ቀን የሚከበርበትን ወቅት ለመምረጥ ጥናት ስለመደረጉም ገልጸዋል። በዚህም መሠረት በዘመናዊ የመንግሥት አሥተዳደር ውስጥ የሀገር መከላከያ ሠራዊት በቋሚነት ተደራጅቶ እንደተቋም የተመሠረተበትን ቀን የሠራዊት ቀን በዓል ለማድረግ ተመራጭ ኾኖ ተወስዷል ነው ያሉት።
በዚህም መሠረት “ዐጼ ምኒልክ የጦር ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት ያቋቋሙበት እና ሚኒስትር የሰየሙበት ቀን የሀገር መከላከያ ሠራዊት ቀን ኾኖ እየተከበረ ነው” ብለዋል ፊልድ ማርሻሉ።
ይህ ታሪካዊ ቀን ጥቅምት 15/1900 ዓ.ም ነበር። ለዚህም ነው የሀገር መከላከያ ሠራዊት ቀን በየዓመቱ ጥቅምት 15 እንዲኾን የተወሰነው ብለዋል።
የሀገር መከላከያ ሠራዊት ቀን በዚህ ታሪካዊ ቀን መከበሩ ቀደምት ጀግኖችን ሞዴል ያደረገ፣ ከቀደምቶች ታሪክ የሚማር እና የሀገር አለኝታ የኾነ ሠራዊት ለመገንባት ስለማስቻሉ ፊልድ ማርሻሉ አመላክተዋል።
ዜናው የአሚኮ ነው
- “አሜሪካን አገር ሆነው የኢትዮጵያ ሰላም የሚያውኩ ተላልፈው ይሰጡኝ” ፖሊስ በኤርቪን ማሲንጋን በኩል ጥያቄ አቀረበአሜሪካ ተቀምጠው የኢትዮጵያን ሰላም የሚያውኩ ተፈላጊዎችን ሀገሪቱ አሳልፋ በመስጠት ትብብር እንድታደርግ የፌደራል ፖሊስ መጠየቁ ተገለጸ። በጀርመን በተመሳሳይ ስራ… Read more: “አሜሪካን አገር ሆነው የኢትዮጵያ ሰላም የሚያውኩ ተላልፈው ይሰጡኝ” ፖሊስ በኤርቪን ማሲንጋን በኩል ጥያቄ አቀረበ
- ሃሰተኛ የተባሉ የዩቲዩበር ባለቤቶች ተያዙ፤ በአንድ ተጠርጣሪ ብቻ ስምንት የዩቲዩብ ቻናል ተከፍቷልፈቃድ ሳይኖራቸው በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስምንት አማረ እና ቤተሰቦቹ በተባለ ህንፃ ላይ ቢሮ ተከራይተው ሃሰተኛና የፈጠራ ወሬ… Read more: ሃሰተኛ የተባሉ የዩቲዩበር ባለቤቶች ተያዙ፤ በአንድ ተጠርጣሪ ብቻ ስምንት የዩቲዩብ ቻናል ተከፍቷል
- “ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋግጠዋል”፤ የሚለው ዜና የአማራ ፖለቲካን ቀየረበሱዳን ለአንድ ዓመት የዘለቀው የእርስ በእርስ እልቂት ብዙ ተዋንያኖች አሉበት። ከአርቡ ዓለም፣ ከአውሮፓ፣ ከአፍሪቃ፣ ሩሲያና አሜሪካንን ጨምሮ የተለያዩ… Read more: “ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋግጠዋል”፤ የሚለው ዜና የአማራ ፖለቲካን ቀየረ
- የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ“ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ” እያሉ በስሟ ሲምሉ የነበሩ ብዙዎች ነበሩ፤ ከልባቸው ለቃላቸው ታምነው ልጅ የሆኗት ግን ጥቂቶች ብቻ ናቸው። አንዳንዶች… Read more: የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ
- አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ“ወገኖቼ እንማርና እናስተምር፣ ወንጀልን እንጸየፈው፣ እንጥላው፣ ወንጀልን ተጸይፈን ወንጌልን እንውደደው፣ በወንጌል እንኑር፣ ወንጌል ሕጓም ስርዓቷም ያማረች ናት፤ ወንጌላዊ… Read more: አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ