በ1983 ኢህአዴግና ሻእቢያ አዲስ አበባ ሲገቡ የኢትዮጵያን መከላከያ ሰራዊት ከሙሉ መዋቅሩ ጋር “የደረግ” በሚል አፍርሰውት እንደነበር ይታወሳል። ባህር ሃይልና አየር ሃይልን ጨምሮ መከላከያ ዳግም በሪፎርም እንዲደራጁ ከተደረገበት ከዛሬ አምስት ዓመት ጀመሮ በተሰራ ስራ ተቋማቱ ኢትዮጵያን በሚመጥን መልኩ መታነጻቸው እየተገለጸ ነው።
ሰሞኑንን 80ኛ የምስረታ በዓሉን እያከናወነ ያለው አየር ሃይል ” ጥቁር አንበሣ” ከአምስት ዓመት በፊት አዋራ የለበሰ፣ ሞቶ የተገነዘ፣ የተረሳና ምናምንቴ ሆኖ የተጣለ ተቋም ነበር። ለውጡን ተከትሎ አየር ሃይል አዋራው ተጠርጎ፣ ዳወው ተመንጥሮ ነብስ መዘራቱን አንደበት ብቻ ሳይሆን ተግባሩ የሚተርከለት ተቋም ሆኗል።
ዘመናዊ ትጥቅ መታጠቁ ብቻ ሳይሆን በብቃትና በሰው ሃይል፣ በጥራትና በጥልቀት የምርመር ተቋም ሆኖ ኢትዮጵያን በአየር ከሚመጣ ማናቸውም አደጋ ለመታደግ ችሏል። ራሱን በሰው ሃይና አደረጃጀት ያዘመነው አይር ሃይል ዛሬ የቀደመውን ውድቀቱን ለሚመኙ ሁሉ ራስ ምታት የሆነ፣ ለአገር ወዳዶች ደግሞ አለኝታ መሆን የቻለ ተቋም መሆኑ ሃላፊዎቹ ሰሞኑንንበተለያዩ መድረኮች ሲያረጋግጡ ሰንብተዋል።
የ”መከላከያ ዘርፍን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች እየተደረጉ ያሉ ማሻሻያዎች ኢትዮጵያን ለማጽናትና ለማስቀጠል ወሳኝ ናቸው ” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የተናገሩትም በዚሁ መነሻ ነው።
የመከላከያ ዘርፍን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች እየተደረጉ ያሉ ማሻሻያዎች ኢትዮጵያን ለማጽናትና ለማስቀጠል ወሳኝ ናቸው ሲሉ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትርና የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዐቢይ አሕመድ ያስታወቁት በዚሁ በሰማንያ ስምንተኛው የምስረታ በዓለ ላይ ነው።
የኢትዮጵያ አየር ኃይል 88ኛ ዓመት የምስረታ በዓል የማጠቃለያ ሥነ-ሥርዓት በቢሾፍቱ አየር ኃይል ጠቅላይ መምሪያ በተካሄደበት ወቅት የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትርና የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዐቢይ አሕመድ፣ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላና ምክትላቸው ጀነራል አበባው ፣ የመከላከያ ሚኒስትር ዶክተር አብርሃም በላይ፣ የተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች አየር ኃይል አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ኢብራሒም ናስር፣ ጄኔራል መኮንኖች፣ የአፍሪካ አየር ኃይል አዛዦች የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። ዝግጅቱ የተከበረበት አግባብ እጅግ ከፍተኛና አህጉርና ዓለም ዓቀፍ ይዘት የተላበሰ በመሆኑ ሰፊ የሚዲያ ሽፋንም አግኝቷል።
የኢትዮጵያ አየር ኃይል 88ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ታላቅ አገር ታላቅ ተቋም የመገንባትና የማጽናት ምልክት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልፀዋል። ኢትዮጵያ የአየር፣ ምድርና ባህርን ጨምሮ በሁሉም መስኮች ወታደራዊ አቅሟን እየገነባች እንደምትገኝ አመልክተዋል።
በኢትዮጵያ የመከላከያ ዘርፍን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች እየተደረጉ ያሉ ማሻሻያዎች አገሪቷን ለማጽናትና ለማስቀጠል ወሳኝ ሚና እንዳላቸው ተናግረዋል።
ለቀጣዩ ትውልድ ታላቅ አገርና ታላቅ ተቋም ለማስተላለፍ መንግሥት አበክሮ እየሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል።
ወቅቱን የዋጀ ወታደራዊ ኃይል መገንባት በአዳዲስ ስልቶች የሚመጡ ጥቃቶችን ለመመከት ያስችላል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለዚህም ሁሉም ወገን የበኩሉን ኃላፊነት እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
የኢፌዴሪ አየር ኃይል አቅሙ እንዲገነባ አስተዋጽዖ ላደረጉ አካላትም ምስጋና አቅርበዋል።
የአየር ኃይሉ 88ኛ ዓመት የምስረታ በዓል “በመስዋዕትነት ሀገርን የዋጀ፤ የኢትዮጵያ አየር ኃይል” በሚል መሪ ኃሳብ ከኅዳር 20 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ሲከበር ቆይቷል።
- ኢትዮጵያ በአሜሪካ የሚኖሩ “ተፈላጊዎች” ተላልፈው እንዲሰጧት ጥያቄ አቀረበችአሜሪካ ተቀምጠው የኢትዮጵያን ሰላም የሚያውኩ ተፈላጊዎችን ሀገሪቱ አሳልፋ በመስጠት ትብብር እንድታደርግ የፌደራል ፖሊስ መጠየቁ ተገለጸ። በጀርመን በተመሳሳይ ስራ መጀመሩ የሚታወስ ነው። ኢትዮጵያ በአሜሪካ… Read more: ኢትዮጵያ በአሜሪካ የሚኖሩ “ተፈላጊዎች” ተላልፈው እንዲሰጧት ጥያቄ አቀረበች
- ሃሰተኛ የተባሉ የዩቲዩበር ባለቤቶች ተያዙ፤ በአንድ ተጠርጣሪ ብቻ ስምንት የዩቲዩብ ቻናል ተከፍቷልፈቃድ ሳይኖራቸው በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስምንት አማረ እና ቤተሰቦቹ በተባለ ህንፃ ላይ ቢሮ ተከራይተው ሃሰተኛና የፈጠራ ወሬ ሲያሰራጩ ነበሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች መያዛቸው… Read more: ሃሰተኛ የተባሉ የዩቲዩበር ባለቤቶች ተያዙ፤ በአንድ ተጠርጣሪ ብቻ ስምንት የዩቲዩብ ቻናል ተከፍቷል
- “ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋግጠዋል”፤ የሚለው ዜና የአማራ ፖለቲካን ቀየረበሱዳን ለአንድ ዓመት የዘለቀው የእርስ በእርስ እልቂት ብዙ ተዋንያኖች አሉበት። ከአርቡ ዓለም፣ ከአውሮፓ፣ ከአፍሪቃ፣ ሩሲያና አሜሪካንን ጨምሮ የተለያዩ አካላት የሚዳክሩበት በዚህ ጦርነት የትግራይ… Read more: “ከሱዳን ተፋላሚዎች ጀርባ ትህነግ መኖሩን ጌታቸው ረዳ አረጋግጠዋል”፤ የሚለው ዜና የአማራ ፖለቲካን ቀየረ
- Are Tigray mercenaries fighting in conflict-ravaged Sudan?Mercenaries from Ethiopia’s Tigray People’s Liberation Front are fighting alongside Sudanese army regulars against fighters of the Rapid Support Forces (RSF), the paramilitary… Read more: Are Tigray mercenaries fighting in conflict-ravaged Sudan?
- Sudan’s RSF Accuse Tigray People’s Liberation Front of Backing SAFSudanese warring party Rapid Support Forces has officially accused the Tigray People’s Liberation Front Fighters of fighting in Sudan in support of the… Read more: Sudan’s RSF Accuse Tigray People’s Liberation Front of Backing SAF