Site icon ETHIO12.COM

” ከሶማሊላንድ ጋር ስለተደረገው ስምምነት የሚመለከታቸው አገራና ተቋማት ቅድሚያ እውቅና ነበራቸው”

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ብሄራዊ ደህንነት አማካሪ ሬድዋን ሁሴን ስለ ኢትዮጵያ እና ሶማሌላንድ የመግባቢያ ስምምነት ምን አሉ ?

„ ኢትዮጵያ ከባህር በር ጋር በተያያዘ ዕድል ያላት የሚመስለው ከሰሜን በኩል ነበር።

ሁሉም ሰው ስለ ባህር በር ሲወራ ቀይ ባህር ነው፤ ስለ ባህር ሲወራ ኤርትራ ነው ፤ ስለ ባህር ከተወራ አሰብ ነው። ይሄን አሁን ለመገልበጥ የሚያችል አዲስ አቅጣጫ ነው የወሰድነው።

ኢትዮጵያ ዙሪያዋ እድሎች አሏት፣ ዙሪያዋ ያሉ እድሎችን መጠቀም የሚያስችል አቅምም አላት፤ መጋራት የሚያስችል በጎ ፍላጎትም መነሻም አላት።

በአንድ ወይ በሌላ መንገድ ኢትዮጵያ አንድ የሆነ የባህር በር ሊኖራት ይገባል በሆነ መንገድ የሚለው ብዙዎች እየገዙት የመጣ ነው።

አትጋጩ፣ ችግር አትፍጠሩ፣ በሰላማዊ መንገድ የሚመጣበትን መንገድ በትዕግስት ሂዱ ነው እንጂ የሚለው ኢትዮጵያ unfair የሆነ ነገር እየፈለገች ነው የሚል ብዙ ምልከታ የለም።

ኢትዮጵያ ፍላጎቷን፣ ያላት concern ትክክል ነው፣ የህዝብ እግደቷም ትክክል ነው፣ ኢኮኖሚዋም ትክክል ነው ፣ የቀጠናው ችግር ትክክል ነው በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ በአውንታዊነት ሚና ልጫወት ማለቷ ተገቢ ነው የሚለውን አጀንዳ ማድረግ ተችሏል።

… ይሄንን ፊርማ (ከሶማሌላንድ ጋር) እስክንፈርም ድረስ በUN ተቋማትም፣ በአንዳድን ትላልቅ ሀገሮች የመረጃዎችም ፣ በእኛ Think tank በሚባሉ NGOዎችም ይሰራ የነበረው ጥናት የኢትዮጵያ መንግሥት ወይ ኤርትራን ይወራል፣ ወይ ደግሞ ሶማሌላንድን በአውዳል ግዛት በኩል ረብሻ ፈጥሮ ቀጠናውን ያተራምሳል የሚል ጥናት ነበር ሲሰራ የነበረው።

በዚህ ላይ draft ቀርቦ የቀረበው draft official ከመሆኑ በፊት የተመለሰ draft እናውቃለን። ይሄንን እነማን እንደሚሰሩት እናውቃለን፣ እሱ ውስጥ #ኢትዮጵያውያን እንዳሉበትም እናውቃለን። ስለዚህ ትላልቆቹ ሀገራት የሳቱት ነገር ፤ እኛም ባገኘናቸው ቁጥር ጦርነት አንፈልግም ውጊያ አንፈልግም ሲባል ‚ አይ መዋጋታችሁማ አይቀርም አናምናችሁም ‚ የሚባል ነው ጭቅጭቁ ከዋሽንግተን እስከ ሌሎቹ ድረስ ፤ ስለዚህ በዚህ ሊዋጉ ነው ብለው ሲገምቱ በዚህ በኩል በሰላም መጣን አልተገመትንም ግን ያልተገመትነው ለበጎ ነው።

… መንግሥት ፍላጎቱን ይፋ ካደረገበት ጊዜ ጀምሮ ለጎረቤት ሀገሮች ፣ በአጠቃላይ ለምስራቅ አፍሪካ ሀገሮች ከአንዴም ሁለት ጊዜ envoy ተልኳል። የማያውቁት ነገር ቢኖር ሙሳቤሂ መቼ እንደሚመጣ (ወደ አዲስ አበባ) እና እዚህ ውስጥ የሼር ጉዳይና የእውቅና ጉዳይ MoU ውስጥ እንደሚካተት አያውቁም። ስለዚህ ከሞላ ጎደል አሰብ አካባቢ የምንከራተት አድርገው ስለወሰዱ ይሄን ጉዳይ ትርጉም አልሰጡትም።

አሁን አፍጥ ሲመጣ ነው ሰው የደነገጠው እንጂ የአብዛኛው ሰው ፍርሃት #በአሰብ በኩል ችግር ትፈጥራላችሁ ፣ ስለዚህ እጃችን ላይ በቂ ችግር አለ የዩክሬን አለ የጋዛ አለ፣ ከምትጨምሩብን በሰላማዊ መንገድ አድርጉትና በሰከነ መንገድ እኛም እናግዛችኃለን የሚል ነውና የpredictability deficit የተነሳበት angle ትክክል አይመስለኝም።

ዜናው የቲክቫህ ነው

Exit mobile version