Site icon ETHIO12.COM

አልሲሲ የሱዳን እንግዳ አይደለም፤ የጥቂት ሆዳም ጀነራሎች…

ሀቀኛ ሱዳኖች ዛሬም ለግብፅና፤ ለተላላኪየሱዳን ጀነራሎች፤ አቋማቸውን አሳውቀዋል !.ትናንት ወደሱዳን የመጣው የግብፅ መንግሥት፣ በሱዳናዊያን፣ ግብዣ አይደለምየመጣው፤ በትንሽ ጀነራሎችና ሱዳንን በገንዘብ በሸጠችው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሯ ግብዣ ነው። ስለዚህ የትናንቱ የአብደል ፈታህ ሲሲ የሱዳን ጉብኝት፣ የሱዳን ህዝቦችን ጋር የሚያገነኛው ነገር የለም። እውቅናም አልሰጠነውም።

የሱዳን ዶክተሮች ማህበር ሊቀመንበሩ ዶክተር ሰይድ እብራሒም በአልጀዚራ ላይ ቃል በቃል የተናገረው ።.ንግግሩን ማሳለጥ ጀመረ፣ ወትሮም ስሙን አንድ ጊዜ የፊራኡን ጥጃ፤ ሌላ ግዜ የፈረንጆች ሹልኪት፣ እያለ የሚጠራው አልጀዚራ፣ አልሲሲን እያጠበ የሚያሰጣለት የፖለቲካ ሊቅ አግኝቷል። የጋዜጠኛው ጥያቄና የእንግዳውን መልስ በዚህ አላቆመም፣ .

«..ጥያቄ ጋዜጠኛ፦ ዶክተር የግብፅ መንግስት ሱዳንን ሊጎበኝ ሲመጣ፤ የሱዳን ህዝብ ግን እንኳን ደህና መጣህ አላለውም በሱዳን ታሪክ አንድ የሌላን አገር መሪ( እንግዳ) እንደዚ አድርጋ ተቀብላ አታውቅም፣ ይሄ የሆነበት ምክኒያት ምንድን ነው ..» ?

መልስ Dr ሰይድ ኢብራሂም፦እኛ አልጠራነውም፣ የሱዳን ህዝብ እንግዳ ተቀባይ ነው። ትናንት ግን ወደ አገራች የመጣው እንግዳ ለኛ እንግዳችን አይደለም፣ አልጠራነውም፤ የጠሩት ትንሽ ጀነራሎችና በሆዷ የምታስበው፣ የውጭ ጉዳይ ሚነስቴሯ መሬም ሳዲቅ አል መሃህዲ ናቸው ። እነዚህ ሰዎ እኛን ወክለው አይደለም፣ የግብፅን መንግስት የጠሩት ሆዳቸውን ወክለው ነው አገራችንን እንዲጎበኝ የጠሩት፤ የሱዳንን ህዝብ የሚወክሁ በሆነ፣ በግብፅ መንግስት የተያዙ ሦስት ትልልቅ ግዛቶችን ነበር መጀመሪያ የግብን መንግስት የሚጠይቁት አለ.

ጥያቄ ጋዜጠኛው፥ እነሱ ያደረጉት ውይይት ለሱዳን አይጠቅምም ብለህ ታስባለህ.? .

መልስ Dr ሰይድ ኢብራሂም፦ ከግብፅ የሚመጣው ስምምነት፤ «.. የገፋፊነትና የበዝባዥነት..». ስምምነት ነው። የሱዳንን ምርቶች እየሰበሰበች ግብፅ አመረተች ብላ ለአለም ትሸጣለች። ሱዳን ምንም ፍብሪካ የላትም፣ ሱዳን አምራች ግብፅ ሻጭ ናቸው፣ ይሄንኑ ሱዳንን ማቆርቆዝ ላይ የተመሰረተ ፖሊሲ ይዞ ሱዳን ለመጎበኝ የመጣውን መንግስት ነው ትናንት አንፈልግህም ውጣ ታገራችን ብለን ባደባባይ የተቃወምነው።.

ጥያቄ ጋዜጠኛው፦ ሱዳን አሁን ከግብፅም ከኢትዮጵያ ጋር የቆየ የድንበር ይገባኛልጥያቄ አላት፤ ከግብፅ ጋር ያለው ጥያቄ ትታኢትዮጵያ ላይ ብቻ አፍጣለች፣ በዚህ ዙሪያ የናተ አቋም ምንድን ነው .?

መልስ DR ሰይድ ኢብራሂምኢትዮጵያ የአል ፋሽጋ መሬት የኢትዮጵያ ብቻ ነው አላለችም። በድንበሩ ዙሪያ እንወያይና ችግራችንን በውይይት እንፍታ ነው ያለችው። ግብፅ ግን ሃላይብና ሻላቲን የግብፅ እንጅ የሱዳን አይደሉም ብላ ለአፍሪካ ህብረት ካርታ ሰርታ እንዲያፀድቅላት አቅርባለች። ስለዚህ ከኢትዮጵያ ጋር ያለው ጥያቄ በውይይት የሚፈታ ሲሆን ይሄንን ቀላል ጥያቄ ነው አለ። የኛ ትልቁ ጥላታችን የግብፅ መንግስት ነው። ሱዳንን በማዳከምና፣ የምንግዜም የግብፅ ገባሪ ሱዳንን መፍጠር ነው የግብፅ ትልቁ ህልም። ለዚህም ነው እኛ ከግብፅ የሚመጣን ስምምነት፤ ከግብፅ የሚመጣ ስምምነት አምርረን የምንቃወመው አለ።

ትርጉም ሱሌማን አብደላ

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=979802275887800&id=100015741093607.ሱሌማን አብደላ

Exit mobile version