Site icon ETHIO12.COM

ፕሮፈሰር ናስር ሀዲ“የሱዳንና መንግስት የቆመው ለግብፅ ጥቅም እንጅ ለሱዳን ጥቅም አይደለም”

የሱዳን ምሁራን የሱዳንን መንግስት አቋም በግልፅ እየተቃወሙ ይገኛል!!!!

ፕሮፈሰር ናስር ሀዲ ይባላል፣ ሱዳናዊ ነው::
በአል ሹሩቅ ቴሌቪዥን ቀርቦ በስሜት ይህን ተናግሯል::

የሱዳንና መንግስት የቆመው ለግብፅ ጥቅም እንጅ ለሱዳን ጥቅም አይደለም። ትክክለኛ የሱዳን ህዝብ ጥቅም ያለው #ኢትዮጵያ ከምትገነባው፣ የህዳሴ ግድብ ጋር ነው!!!

የሱዳን መንግስት አቋሙ የኛ የሱዳን ህዝቦች አቋም አይደለም!!! ለግብፅ ጥቅም መከበር ነው የቆመው። ግብፅ ስትመኘው የነበረውን አይነት መንግስት በሱዳን በቅሎላታል። ይሄ መንግስት የግብፅን ጥቅም ለማስከበር #አጎብድዶ እየሰራ ነው። እንጅማ፣ በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ የሱዳን አቋም ከግብፅ ጋር እንዴት አንድ አይነት ሊሆን ቻለ? ሲል ፕሮፌሰሩ ይጠይቃል። የግብፅ ፍላጎት ከአባይ ወንዝ 50 % መውሰድ ነው። ኢትዮጵያ 30% ትወሰድ ሱዳን 20% ይበቃታል፣ እኔ እሱዳን መሬት ላይ እየመጣ አልምቼ የግብፅ ምርት ብየ እሸጣለሁ የሚል አቋም ነው ያላት። አሁን የኛ መንግስት ይሄን አቋም ደግፎ ነው የሱዳንና የግብፅ ፍላጎት እየተባለ በሚዲያ የሚነገረን፣

ፕሮፌሰሩ ንግግሩን አላቆመም፣ ግብፅ የህዳሴ ግድብን የምትፈራው ለሱዳን ጥቅም ስለሚውል ነው፡፡ ምክኒያቱም ግድቡ ከተጠናቀቀ ግብፅ እንደፈለገች የሱዳንን ድርሻ መውሰድ አትችልም። በተረፈው ድርሻዋን ለፈለገችው ልማት ማዋል ትችላለች።

የህዳሴው ግድቡ ሲጠናቀቅ የሚፈልገውን ሁሉንም ሀይል ያቀርባል ፣ የሱዳን የኢንዱስትሪ መጠን ይጨምራል፡፡ ንግድና ኢንቨስትመንቶች ይጨምራሉ። ያማለት የሱዳን ኢኮኖሚ ተነቃቃ ማለት ነው። ሱዳን አምራች ግብፅ ሻጭ የምትሆንበት የዘመናዊ ቅኝ ግዛት (የ Modern Colonialism) ህልሟ አከተመ ማለት ነው።

እናም ግብፅ የምትፈራው የአባይን ግድብ መገደብ ብቻ ሳይሆን፣ በግድቡ ሱዳን ተጠቃሚ ሆና ትነቃብኛለች፣ እኔ እንደፈለኩ የሱዳንን ምርት እየሰበሰብከ አልቸበችብም ወይም ዘመናዊ የቀኝ አገዛዝ ህልሜ ይቋረጥብኛል ብላ ስለምታስብ ነው። ብሏል ሱዳናዊው ፕሮፌሰር!!!!

ትርጉም ሱሌማን አብደላ

Exit mobile version