Site icon ETHIO12.COM

ሩሲያ በግድቡ ዙሪያ ያሉ አለመግባባቶች በአፍሪካ ህብረት ማዕቀፍ ስር እንዲፈቱ እንደምትደግፍ አስታወቀች


በግብጽ ለሁለት ቀናት የስራ ጉብኝት ያደረጉት የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ ከግብጽ አቻቸው ሳሚ ሽኩሪ ጋር በመሆን በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ፤ ሳሚ ሽኩሪ ኢትዮጵያ ሁለተኛው ዙር የውሃ ሙሊትን ለማከናወን ማቃዷን በማጣቀስ “የተናጠል እርምጃ እንዳይወሰድ ሩሲያ ጫና እንደምታሳድር እንትማመናለን” በሚል ቢናገሩም፤ የሩሲያው አቻቸው በተቃራኒው አገራቸው የአፍሪካ ህብረትን የድርድር መንገድ እንደመትደግፍ አስታውቀዋል።

የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ በዚሁ መግለጫ ላይ እንደተናገሩት፤ ሩሲያ በሶስቱ አገራት መካከል እየተካሄደ ባለው ድርድር አልተጋበዘችም። ይሁን እንጂ በአፍሪካ ህብረት ማዕቀፍ ስር የሚካሄደውን ድርድር ደግፋለች፤ ትደግፋለችም ማለታቸውን አሶሼትድ ፕሬስ በዘገባው ገልጿል።

በሶስት አገራት መካከል ያለውንና ረጅም ጊዜ ያስቆጠረውን አለመግባባት ለመፍታት መፍትሄው በአፍሪካ ህብረት መሪነት እየተካሄደ ያለው ድርድር መሆኑን የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በዚያው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ በአጽንኦት ተናግረዋል።. (ኢ ፕ ድ)


Exit mobile version