Site icon ETHIO12.COM

የአሜሪካ ኤምባሲ የሰላማዊ የተቃውሞ ጥሪውን ጠምዝዞ የማስጠንቀቂያ መልዕክት አሰራጨ

“ብሔራዊ ክብር በህብር” በሚል መሪ ቃል በኢትዮጵያ ላይ የተከፈተውን ዘመቻ በተቀናጀ መልኩ በአገር ቤትና በውጭ አገር ለመቃወም የቀረበውን ጥሪ ተከትሎ የአዲስ አበባ አሜሪካ ኤምባሲ የማስጠንቀቂያ መግለጫ አሰራጨ።

አሜሪካ በተለያዩ ወሳኝና አስቸጋሪ ጊዜያት ኢትዮጵያን በመክዳትና ለጠላት አሳልፋ በመስጠት የምትታወቅ አገር ናት። የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት መታረዱን፣ ትጥቅ የፈታው በትራክ መጨፍለቁን፣ ትህነግ ይህ ሳያነሰው በማይካድራ ንጹሃንን ቀደሞ በመዘጋጀት አርዶ መሰወሩን እያወቀች ድርጊቱን ከማመን በዘለለ የወሰደችው አንዳችም አቋም አለመኖሩ ዜጎችን አሳዝኗል። የተባበሩት መንግስታትን ሃላፊነት ወስዶ ለሰላም አስከባሪነት በአፍሪካ የተሰማራውን የአገር መከላከያ ሰራዊት በጅምላ ሲታረድ ምንም ያላለችው አሜሪካ በተገላቢጦሽ እየወሰደች ያለው አቋም አግባብ አለመሆኑንን ለመቃወምና ደብዳቤ ለማሰራጨት የተደረገውን ጥሪ መልኩን ማስቀየር ለምን እንደተፈለገ አብዛኞችን ግር አሰኝቷል።

Related stories   መካከለኛዉ ምሥራቅ ሌላ ዘመን ሌላ ጥፋት

ኤምባሲው ጉዳዩን አጋኖና ለተጀመረው ኢትዮጵያን የማጥፋት ሃሳብ እንደ ግብአት ተጠቀሙበት እንጂ የተላለፈው ጥሪ ” ህዝቡ ህግና ስርዓትን በተከተለ መልኩ በየኤምባሲዎች አቅራቢያ በመገኘት ድምጹን ማሰማት ይችላል” የሚል ሲሆን ጥሪውን ያሰሙት ከአስተባባሪ ኮሚቴው ውስጥ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ፣ ዑስታዝ አቡበክር አህመድ፣ አርቲስት ዘለቀ ገሰሰን ጨምሮ ሌሎችም ታዋቂ ኢትዮጵያውያን እንደሚገኙበት ተጠቅሶ ነበር።

በዚህ ግልጽና ሰላማዊ የተቃውሞ ጥሪ መነሻነት ነው ኤምባሲው አገልግሎት እንደማይሰጥ ቀኑንን ጠቅሶ ያስታወቀው። ሰዎችም ከኤንባሲው አካባቢ ራሳቸውን እንዲያረቁ ያሳሰበው። በአንድ ከተማ ውስጥ አገር ከልሎ የያዘው የአሜሪካ ኤምባሲ ሰላማዊው ተቃውሞ ለምን እንዳስጨነቀው ግን ይፋ አላደረገም።

“ድንገት ሊከሰት የሚችል ጉዳይ ካለ ሚዲያ ተከታተሉ፣ ሰው የበዛበት አካባቢን ተጠነቀቁ፣ አካባቢያችሁን ነቅታችሁ ተከታተሉ፣ ህግን አክብሩ” ሲል ዜጊቹ ለሆኑት ጥሪ ያሰራጨው ኤንባሲው፣ ይህን ያሰራጨው ነገ የተቃውሞ ስለፍ በተለያዩ ኤምባሲዎች ዘንድ እንደሚደረገ በማህበራዊ ሚድያዎች እየተሰራጨ መሆኑንን ጠቅሶ ነው። ኤምባሲው በምን መነሻ ይህን እንዳለ ባይታወቅም ጥሪው በኦፊሳል በሚታወቁ ተጸኖ ፈጣሪ ወገኖች፣ በአገሪቱ ብሄራዊ ሚዲያዎችና ይህንን ለማስተባበር “ብሔራዊ ክብር በህብር” በሚል መሪ ቃል የሚመራዉን የተቃውሞ ዘመቻ በሚመሩ አካላት ነው።

የዘመቻው የህዝብ ግንኙነት አስተባባሪ አቶ አብይ ታደለ ” እስከ መጪው አርብ ባሉት ጊዜያት በተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆችን በማስተባበር በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ ለመግባት የሚሞክሩ የውጭ ሀይሎች እጃቸውን እንዲያነሱ የሚጠይቅ ፊርማ ይሰበሰባል። እንዲሁም፣ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ላደረጉ የተለያዩ ሀገራት ኤምባሲዎች የወከሏቸውን ሀገራት በኢትዮጵያ ጉዳይ ጣልቃ ከመግባት እንዲቆጠቡ የሚጠይቅና የኢትዮጵያውያንን አቋም የሚገልጹ ደብዳቤዎች እንዲደርሳቸው ይደረጋል” ሲሉ ነበር ጥሪያቸውን በይፋ ያሰሙት።

አቶ አብይ አክለውም፣ ከቀኑ 10 ሰዓት እስከ 11 ሰዓት ባለው ጊዜ “ከኢትዮጵያ ላይ እጃችሁን አንሱ” የሚል መፈክር በመላው ሀገሪቱ እንዲሁም በተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች እንዲስተጋባ ይደረጋል። በመጨረሻም ከምሽቱ 12 ሰዓት የዕለቱ መርሃ ግብር ማጠቃለያ እና የአጠቃላይ ዘመቻው መክፈቻ የሆነውን የኪነ-ጥበብ ዝግጅት ይካሄዳል ብለዋል። ህብረተሰቡ የኮሮና ቫይረስ መመሪያዎችን በጥንቃቄ በመተግበር የዘመቻው ተሳታፊ እንዲሆኑም አስተባባሪዎቹ ጥሪያቸውን አስተላለፈው ነበር።

ህዝቡ ህግና ስርዓትን በተከተለ መልኩ በየኤምባሲዎች አቅራቢያ በመገኘት ድምጹን ማሰማት ይችላልም ተብሏል።በአስተባባሪ ኮሚቴው ውስጥ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ፣ ዑስታዝ አቡበክር አህመድ፣ አርቲስት ዘለቀ ገሰሰን ጨምሮ ሌሎችም ታዋቂ ኢትዮጵያውያን ይገኙበታል።

ኤምባሲው አዲስ አበባ ተቀምጡ ሰላማዊውን ተቃውሞ ቢጠመዝዘውም አዘጋጆቹ ፕሮግራሙ ቀደም ሲል በተባለው መሰረት እንደሚካሄድ በድጋሚ በመንግስት መገናኛዎች ይፋ አድርገዋ።

የኤምባሲውን ማስጠንቀቂያ መንግስትንና ጥሪውን ያቀረቡትን ወገኖች ለማሸማቀቅ፣ እንዲሁም የተቃውሞውን መጠን ለማቀዛቀዝ ዒላማ ያደርገ እንደሆነ በማህበራዊ ገጾቻቸው የጻፉ አሉ። በሌላም በኩል ሰላማዊውን አንገራዊ ጥሪ ዓላማውን በማሳት ወደ ሃይልና ባንዲራ ማቃጠል ጥሪ አዙረው ሲያበቁ አስተባባሪዎቹ ባንዲራ እንዲቃጠልና በኤምባሲዎች ላይ ጥቃት እንዲፈጸም ጥሪ እንዳሰራጩ ተደርጎ በማህበራዊ ገጾች የሚያሰራጩ ታይተዋል። ስምና አድራሻ እየጠቀሱም በሌለ ጉዳይ ኢትዮጵያ ላይ ላሴሩ አገራት ተቆርቋሪ ሆነው መርጃ ሲሰጡ የነበሩም ተስተውለዋል።


Exit mobile version