ከትግራይ ክልል በስምንት መኪናዎች ተጭኖ በህገ ወጥ መንገድ ሊወጣ የነበረ 800 ኩንታል የዕርዳታ እህል አዲ ጉደም ኬላ ላይ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አሰተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
በድርጊቱ የተሳተፉ ተጠርጣሪዎችን በህግ ጥላ ስር አድርጎ እያጣራ እንደሚገኝም ኮሚሽኑ ገልጿል። የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አሰተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር መንግስትአብ የማነ ለኢቢሲ እንደገለጹት፤ በክልሉ ለስብዓዊ ድጋፉ የመጣውን የእርዳታ እህል ከተረጂው ሰው ጎሮሮ ቀምተው ለግል ጥቅማቸውና ብልፅግናቸው ሲሯሯጡ የነበሩ ነጋዴዎች ናቸው፡፡
ከእነዚህ ሰዎች ጀርባ የነበሩ እነማን እንደሆኑ ፖሊስ በምርመራ እያጣራ ይገኛል። በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የፀጥታና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ረዳት ኮሚሽነር የማነ ገሰሰው በበኩላቸው ተደራጅተው እህልን ከዚህ አከባቢ በመግዛት ወደ ተለያዩ ቦታዎች በመውሰድ እጥረት በመፍጠር በትግራይ ረሃብና ችግር እንዲፈጠር የሚያደርጉ አካላት መኖናረቸውን ገልጸዋል፡፡
የወንጀል አፈጻጸሙ በተደራጀ መንገድ መሆኑንም የገለጹት ረዳት ኮሚሽነሩ፤ በዚህ ህገ ወጥ ድርጊት ውስጥ በየዋህነት የሚሳተፉ ባለሞያዎች ጥንቃቄ እንዲያደርጉም አሳስበዋል፡፡ ከዚህ በፊት በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረው ሶስት ሺህ ኩንታል የእርዳታ ዕህል መያዙን የገለጸው ፖሊስ በወንጀል ድርጊቱ የተሳተፉ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ሆነው ምርመራ እየተደረገባቸው ይገኛል፡፡
እንደ ኮሚሽነሩ ገለጻ፣ ከዚህ የከፋ ችግር ስለሌለ ህብረተሰቡ በንቃት መሳተፍ ይኖርበታል፡፡ ከህገ ወጥና ስግብግብ ነዳዴዎች በስተጀርባ ያለ ማንኛውም አካል ከህግ ተጠያቂነት እንደማያመልጥ ማወቅ ይኖርበታል ብለዋል፡፡ የመቀለ ከተማ ጊዜያዊ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጂነር ግዛው ሐጎስ በበኩላቸው፣ ይህ ህገ ወጥ ተግባር በመጀመሪያው እርዳታ አሰጣጥ ላይ መከሰቱን ጠቅሰው በሁለተኛው ዙር ላይ ይሄ እንዳይደገም በጥብቅ ቁጥጥር እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል።
- የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ“ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ” እያሉ በስሟ ሲምሉ የነበሩ ብዙዎች ነበሩ፤ ከልባቸው ለቃላቸው… Read more: የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ
- አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ“ወገኖቼ እንማርና እናስተምር፣ ወንጀልን እንጸየፈው፣ እንጥላው፣ ወንጀልን ተጸይፈን ወንጌልን እንውደደው፣… Read more: አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ
- ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናውቤት የተባለች አንዲት ሴት እንዲህ ብላለች፦ “ደም ማነስ የያዘኝ በአሥራዎቹ… Read more: ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናው
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት