Site icon ETHIO12.COM

ትግራይን አገር ለማድረግ የተላለፉ ዓለም አቀፋዊ፣ ቀጠናዊና ሀገራዊ ስትራቴጅያዊ ውሳኔዎች ተጋለጡ፤ ግድቡን ማፍረስ ይገኝበታል

በአጠቃላይ ሀገረ ትግራይን ለመመስረት አሁን ያለው የኤርትራ፣ የኢትዮጵያ፣ የሶማሊያ፣ የጅቡቲ ቅርፅ መቀየር አለበት። እነዚ ሀገሮች መልካቸው ካልቀየሩ ግን ትግራይ ለብቻዋ ተነጥላ ሀገር ለመሆን የሚቻል አይደለም። ለትግራይ ሀገር መሆን ከ4 ሀገሮች ጋር ጥብቅ ዝምድና ያስፈልጋል። እነሱም ግብፅ፣እስራኤል፣እንግሊዝና አሜሪካ ናቸው። ለግብፅ በአባይ ጉዳይ መወያየት። ሀገረ ትግራይ እንድትመሰረት የምትደግፍ ከሆነ አባይ በወታደራዊ ስሪት በትግሬዎች አቅም እንዲፈርስ መደረግ እንደሚቻል የውሳኔ ሐሳብ ማቅረብ።

አሸባሪው ህወሓት በሚስጥራዊ ስብሰባ ኢትዮጵያ ውስጥ ግጭት በማስነሳት ትግራይን እንደ ሀገር ለመመስረት ያስችላሉ ብሎ ያስተላለፋቸው ዓለም አቀፋዊ፣ ቀጠናዊና ሀገራዊ “ስትራቴጅያዊ ውሳኔችን የኢፕድ ምንጮች አድርሰውናል

በተለያዩ ሀገሮች የተሰባሰቡ የአሸባሪው ህወሓት ርዝራዦች ተወካይ ብሔርተኞች ለ6 ቀናት በዙም ተሰብስበው ሰንብተዋል። ተሰብሳቢዎቹ ከውጭም ከሀገር ውስጥም የተካተቱ ሲሆን በረሃ ካሉት የኪዳነ አመነ እና የመሃሪ ዮሃንስ አስተያየት ተደምጧል። የውይይቶቻቸው ዋና ዋና አላማዎች የሚከተሉት ናቸው:_

ሀ) ትግራይ ሀገር እንድትሆን ለማድረግ ሊሰራ የሚገባው ውስጣዊና ውጫዊ የፖለቲካ ስራዎች ለመረዳዳት የሚለው ዋነኛው የስብሰባው አላማ ነው።

ለ) ይሄንን ለማድረግ የተስማሙበት ቅድመ ሁኔታ ትግራይ የጀመረችው ወታደራዊ ጦርነት አሸንፋ እንድትወጣ አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑ ነው። ይህ ካልሆነ፣ ትግራይ ካለችበት የጦርነት አዙሪት ከተሸነፈች ትግራይ እንደ ሀገር ይቅርና መቀሌ የትግራይ ክልል አካል ሆና አትቀጥልም የሚል መደምደሚያ ወስደው ነው ውይይቱን የጀመሩት። በውይይታቸውም በሚከተሉት ነጥቦች የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ ተለያይተዋል።

1) የትግራይ ሀገረ-መንግስትነትን ለመመስረት ኢትዮጵያ ውስጥ ሶስት ዓበይት አብዮቶችን መፈጠር አለባቸው።

2) የኦሮሞ ብሄር ምንም የጋራ አገራዊ ማንነት ስሌለው፣ በሀገራዊ ስሜት ሊነሱ ስለማይችሉም ጭምር የአዲስ አበባን ጉዳይ ምክንያት በማድረግ “ፊንፊኔ ኬኛ” ብለው እንዲነሱ ለማድረግ ከኦነግ ጋር አስፈላጊ ትብብር እንዲፈጠርና ለዚህም ትግሬዎች አስፈላጊውን ዋጋ ከፍለው የፊንፊኔን ጉዳይ በማነሳሳት “የኦሮሚያ አካል ካልሆነች” በሚል ጥያቄ አዲስ አበባ ላይ እሳት መጫር።

3) በአፋርና በሶማሌ መካከል የተፈጠረው ግጭት በማባባስ፣ የአፋር ብሔረሰብ ላይ በትግራይ በኩል ጦርነት እንደሚከፈት በማድረግ extensional threat እንዲሰማው ማድረግ። በሶማሊና በትግራይ መገደል የጀመረ አፋር ሳይወድ በግድ ኤርትራና ጅቡቲ ካሉት አፋሮች ጋር እንዲተባበር ማድረግ። ይሄን ስልት በማፍጠን ከአፋር ጋር የመሬት ጥያቄ በማንሳት ወደ ቀጣዩ ውግያ መግባት። በውግያው የሚያጋጥመው ኪሳራ ወደ ስነልቦና ውድቀት ስለሚመራቸው በኢትዮጵያ ተስፋ ይቆርጣሉ።

4) አፋር ውስጥ የሚነሳ ጦርነት በproxy ወደ ሶማሊ እንዲልም በማድረግ ሶማሊ ክልል እሳት እንዲደፋበት መስራት። ከዚህ በኋላ በጁቡቲና በታላቋ ሶማሊያ ያለውን የሶማሊ ብሔረሰብ በማነሳሳት ኢትዮጵያ ውስጥ ወደ ጦርነት ገብቶ ያለውን የታላቋ ሶማሊያ ሀገር ብሔርተኝነት እንዲያነሳ ቅስቀሳ ማካሄድ

5) የትግራይ ሀገረ የመሆን መንገድ መራመድ ሲጀምር፣ የመሬት የወሰን ጥያቄ ከአማራና ከአፋር ጋር በማንሳት የትግራይ ህዝብ ከነዚህ አህዛብ ጋር ላንዴና ለመጨረሻ የሚለያይበት የስሜት ግንብ መስራት

6) በኤርትራ ጉዳይ ባድሜን በኃይል እንደተወሰደች በማወጅ ጦርነቱ በመክፈት የትግራዋይ ብሔርተኞች ማንሳት። ይሄን የሚያደርጉ ከኤርትራውያን ዲያስፖራ መጠቀም።

7) ከኢሳያስ ውድቀት በኋላ ለሚፈጠር ኤርትራዊ ስነ ልቦና ውድቀት ብሄራዊ ንቃት እንዲኖረው፣ ስልጣን በትግራዋይ ብሄርተኛ እንዲያዝ ማድረግ። ኤርትራ ውስጥ ላለው ትግራዋይ የመጨረሻ እድል መስጠት።

8)ኤርትራ ውስጥ የሚኖረውን ከትግራዋይ ማንነቱ ሊያተሳስረው የሚችል የሽግግር ግዜ ስለሚያስፈልገው መጀመርያ የተለያዩ ማንነቶች ያሏቸውን የኤርትራ ሕዝቦች በማደራጀት በብሄር ፌደራሊዝም የምትተዳደር ኤርትራ እንድትፈጠር መስራት ከዛ በኋላ በተወሰነ ግዜ ውስጥ የትግሬ አንድነት ማረጋገጥ

9) ኤርትራ ውስጥ ያሉትን አፋሮች ኢትዮጵያና ጅቡቲ ካሉት አፋሮች ጋር አብረው የሚሰሩትን ሀገር ለመፍጠር መቀስቀስና መደገፍ

10) በኢትዮጵያ፣ ሶማሊያና ጅቡቲ ያሉ ሶማሊዎች ወደ ትልቋ ሶማሊያ እንዲጨመሩ ማድረግ

11) በኤርትራና በኢትዮጵያ ያሉትን ትግርኛ ተናጋሪ ህዝቦች ታላቋን ትግራይ እንዲመሰርቱ ማድረግ

12) ይቺ አሁን ኢትዮጵያ የምትባለው ሀገር ደግሞ አማራዎች ብቻ ይዛ እንድትቀር ማድረግ

13) በአጠቃላይ ሀገረ ትግራይን ለመመስረት አሁን ያለው የኤርትራ፣ የኢትዮጵያ፣ የሶማሊያ፣ የጅቡቲ ቅርፅ መቀየር አለበት። እነዚ ሀገሮች መልካቸው ካልቀየሩ ግን ትግራይ ለብቻዋ ተነጥላ ሀገር ለመሆን የሚቻል አይደለም። ለትግራይ ሀገር መሆን ከ4 ሀገሮች ጋር ጥብቅ ዝምድና ያስፈልጋል። እነሱም ግብፅ፣እስራኤል፣እንግሊዝና አሜሪካ ናቸው።

14) ለግብፅ በአባይ ጉዳይ መወያየት። ሀገረ ትግራይ እንድትመሰረት የምትደግፍ ከሆነ አባይ በወታደራዊ ስሪት በትግሬዎች አቅም እንዲፈርስ መደረግ እንደሚቻል የውሳኔ ሐሳብ ማቅረብ።

15) ከእስራኤል ጋር በሚደረገው ውይይት የሀገሪቱን የኋላ ሁኔታን በማንሳት ትግራዋይ ተመሳሳይ መንገድ እያለፈ እንዳለ ማሳመን

16) ከእንግሊዝና አሜሪካ ሚደረገው ውይይት ትግራይ ለስነ-ሐሳብ ኒዮ-ሊበራሊዝም የምትቀበል ሀገር እንደሆነች በማሳመን ትግራይ ሀገር ስትሆን የሀገሪቱ መአድኖች በነሱ ሀገር ድርጅቶች እንደሚቆፈር መግባባትና የሁለቱ ሀገሮች NGO ትግራይን ማሳረፍያቸው ማድረግ እንደሚችሉ ማሳመን። በተጨማሪ እነዚህ ሀገሮች በአፍሪካ ቀንድ የሚያወጡትን ፖሊሲ ትግራይ መጀመርያ እንደምትተገብር መቀበል

17) የቻይና እና የሩስያ ጉዳይ ከአሜሪካና ከእንግሊዝ ጋር ሆኖ እንዲፈታ መስራት

18) አሜሪካና እንግሊዝ ላቀረቡት የውሳኔ ሐሳብ ሙሉ በሙሉ መቀበል። ያቺ ወንዝ ልትሻገር የማትችል ጉዳይ የprotestanism ሃይማኖት ተቀበሉ ከሚል ውጭ ያለውን መቀበል።

19) በኤርትራ እያደገ ያለውን የእስልምና መስፋፋትን እንደ ምክንያት በማቅረብ ያለንን ስጋት ማቅረብ፣ በክርስትና ላይ እየደረሰ ያለውን እንደ አጋጣሚ መጠቀም።

ኢፕድ ምንጭ


Exit mobile version