ባልደራስ አዲስ አበባን ከብሄር እሳቤ ውጭ ለማድረግ ማሰቡን ገልጾ ሲነሳ ” በተረኘት ስሜት” የተደናገጡ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ተቀብለውት እንደነበር፣ ከዛ በሁዋላ ብዙም ሳይቆይ ከአብን ጋር መጋባቱ ሙሉ ድጋፍ እንዳሳጣው፣ ከዚያም በላይ የትህነግ አፍ የነበረው ኤርሚያስን ለገሰን ምክትል ሊቀመንበር ማድረጉ ራሱን በራሱ ያከሰመ ያህል እንደጎዳው በተደጋጋሚ ሲገለጽ ነበር።
ኢትዮ12 ከአራት ቀን በፊት ” በሂልተን ሎቢ ባልደራስ ምርጫ ቦርድ ለእስክንድር ደጋፊዎች ተጨማሪ የምዝገባ ጊዜ እንዲሰጠው የመጠይቀ ሃሳብ እንዳለው ማናገሩ ተሰማ” በሚል ርዕስ በጉዳዩ ዙሪያ ዝግጅት ሲደረግ እንደነበርና አስታውቃ ነበር።
ቀደም ሲል ከሂልተን በደረሰ ሪፖርት መሰረት ይህን ጽፈን ነበር
በዘገባው ” ለኢትዮ 12 የአዲስ አበባ ተባባሪ ትዝብቱን የሚያካፍለው የውጭ አገር ጋዜጠኛ እንዳለው ባልደራስ እነ እስክንድር ምርጫ የሚወዳደሩ ያልመሰላቸው ደጋፊዎቻችን ስላልተመዘገቡ ምርጫ ቦርድ ተጨማሪ የመመዝገቢያ ቀን እዲሰጣቸው ለመጠይቅ ማቀዳቸውን ትልቅ ለምትባለዋ አገር ዲፕሎማት ነግረዋል” ነበር ስትል ነበር አምዳችን የአዲስ አበባ ተባባሪዋን ጠቅሳ የጻፈችው።
ዛሬ ኢትዮ ኢንሳይደር የሚባለው የድረ ገጽ ሚዲያ ባልደራስ ዛሬ በራስ አምባ ሆቴል ባካሄደው መግለጫ በርካታ ክሶችን ካቀረበ በሁዋላ፣ የመራጮች ምዝገባ ሂደቱ በበርካታ ችግሮች የተተበተበ መሆኑንን የበጥናቱ አስታውቆ ፓርቲው፤ የምርጫ ካርድ ማውጫ ጊዜ እንዲራዘም በድጋሚ ጠይቋል።
ባልደራስ የመራጮች ምዝገባ ሂደቱ በተጠናቀቀበት ዕለት በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይም ተመሳሳይ ጥያቄ አቅርቦ ነበር። የመጪው ምርጫ የድምጽ መስጫ ቀን ሁለት ሳምንት በቀረው በዚህ ጊዜም፤ ባልደራስ አሁንም ይህን አቋሙን አለመተውን አስታውቋል። የፓርቲው የሰብዓዊ መብት እና የህግ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሔኖክ አክሊሉ፤ “የመራጮች ምዝገባ እንደገና እንዲደረግ ባልደራስ ይጠይቃል” ሲሉ በዛሬው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተናግረዋል። ይሁን እንጂ በሰነድ ጥያቄውን ስለማቅረባቸውና አዎንታዊ ምላሽ ካላገኙ ምን እርምጃ እንደሚወስዱ ይፋ አላደረጉም።
ስለ አዲስ አበባ ያነሳው የባልደራስ መግለጫ ቅድመ ምርጫ ሂደቱ ከእጩዎች እና መራጮች ደህንነት አኳያ ምርጫው “የደህንነት ስጋት” እንዳለበት አመልክቷል። ፓርቲው ለዚህ በማሳያነት የጠቀሳቸው በቢሾፍቱ፣ በመተከልና በጎንደር መተማ ዩሃንስ የተገደሉ የኢዜማ እና የአብን አባላትን ነው። “እነዚህ ግድያዎች የቅድመ ምርጫውን ሂደት ነጻነት እና ፍትሃዊነት አጠያያቂ ያደርገዋል” ሲል ባልደራስ አዲስ አበባ ላይ ላነሳው ጥያቄ ማሳያ አድርጓል።
ኢትዮ 12 ሜይ 23 ቅድመ ዳሰሳ ለሚካሂዱ አባሎቻቸውና የውጭ ሚዲያዎች ኦፊሳል ባልሆነ ስብሰባ US AID፣ አሜሪካን ኤምባሲ፣አሊያንስ ፍራንስ በህብረት ባዘጋጁት የመሰረታዊ መረጃ ማስጨበጫ ውይይት ላይ በስም ጠቅሰው አብንና ባልደራስ ምርጫው ሲቃረብ መመረጣቸውን ሲጠራጠሩ ባለቀ ሰዓት ሊያፈነግጡ እንደሚችሉ መረጃ ጠቅስው መናገራቸውን አስታውቀን ነበር። ከስር ያለውን ያንንቡ
በምዘገባ፣ በቅሰቀሳ፣ በመዘግብ ማጣራት፣ የራት አባላቱ እስር፣ መገናኛ ብዙሃን አጠቃቀም፣ አዲስ አበባ እንግልትና ግርግር እንዳይኖር በሚል ታስቦ 1727 የምርጫ ድምጽ መስጪያ ጣቢያ መኖሩን እንደ ችግር አንስቶ ቸግሩ በ300 የምርጫ ጣቢያ ብቻ ለሰጥ እንደሚገባ በጥናት ማረጋገጡን አውስቷል። በመጨረሻም ምንም እንኳ ምርጫው እንጀን የሞላበት ቢሆንም ሁሉም ወገን ትብብር እንዲያደርግ ጠይቋል። የፓርቲው የውጭ ክንፍ መሪ የሆኑትና የ360 ተንታኝ አቶ ኤርሚያስ ለገሰ ማምሻውን ምን እንደሚሉ አልታወቀም።
ሙሉ መረጃው እንዲኖራችሁ ኢትዮ ኢንሳይደርን እዚህ ላይ በመክፈት ቪዲዮውን ያድምጡ።
- ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናውቤት የተባለች አንዲት ሴት እንዲህ ብላለች፦ “ደም ማነስ የያዘኝ በአሥራዎቹ ዕድሜ ሳለሁ ነው። ቶሎ ይደክመኝ፣ አጥንቶቼን… Read more: ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናው
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ።… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት
- የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡምየፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የትራንስፖርት ስምሪትና የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር ሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ 11 ግለሰቦች በስር ፍ/ቤት… Read more: የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡም
- መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለየአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ ምክንያቱም “የኢትዮጵያ መንግሥት በሕገ ወጥ መንገድ የአውሮፓ ኅብረት… Read more: መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ