Site icon ETHIO12.COM

የG7 ውሳኔ የእነ ቴዎድሮስን ዘመቻ ተስፋ ያመከነ ሆነ፤ “ኢትዮጵያ እፎይ አለች”

World Health Organization Director-General Tedros Adhanom Ghebreyesus looks on during a press conference following an emergency talks over the new SARS-like virus spreading in China and other nations in Geneva on January 22, 2020. - The coronavirus has sparked alarm because of its similarity to the outbreak of SARS (Severe Acute Respiratory Syndrome) that killed nearly 650 people across mainland China and Hong Kong in 2002-03. (Photo by PIERRE ALBOUY / AFP) (Photo by PIERRE ALBOUY/AFP via Getty Images)

በትውልድ ሱዳን በዜግነት እንግሊዛዊ፣ በእንግሊዝ የሲኤንኤን ሪፖርተር ኒማ አልባጊር ክፍል ሁለት ተውኔቷን ያካሄደቸው በዋነናት ሳማንታ ፓወር፣ ሊንዳ ቶማስና ማርክ ሎውኮክን በመያዝ ከአፍሪካና አውሮፓ ኮሚሽን ለዓይነት የተካተቱበት ቡድን በመያዝ የአውሮፓ አሜሪካ የጠረጴዛ ውይይት ለአስቸኳይ እርዳታ በሚል ነበር።

ኒማ እንደ ፊልም አክተር “ ጋዜጠኞች ነን፣ ፈቃድ አለን…” እያለች ዋሻ ዋሻውን ስትዞርና በመወራጨት ከመከላከያ አባላት ጋር የነበራትን ግንኙነት በፊልም እያሳየች በአክሱም ተፈጸመ ያለችውን የዘጠኝ ደቂቃ ትረካ አቅርባ ነበር። በዘገባው የኤርትራ ወታደሮችን ናቸው ያለቻቸውን አሳይታለች። ነገር ግን መንግስት ፈቅዶላት ያነጋገረቻቸውን በሙሉ ድምጻቸውን በመዋጥ ሙያዊ ውሏን የበጠሰች፣ ምግባረ ብልሹና አድረገው ፈርጀዋታል።

READ ALSO THIS የሲኤንኤን ዘጋቢ ኒማ- በተወነችው ተውኔት ውስጥ ዳግም ሞት የተፈረደባቸው ዜጎች

“ሁለት ጉዳዮች ወለል ብለው ይታያሉ” ዋሲሁን ሰማን። ጋዜጠኛዋ መሰረቷ ከሱዳን ነው። የምትኖረውና የተማረችው እንግሊዝ ነው። እነዚህ ሁለት ጉዳዮች አያይዞ ለሚያየው የኒማ ኢልባጊር ዘገባ መነሻና መድረሻ ይገባዋል። ይህ ሊደበቅ የማይችል ጉዳይ ነው። ሲታሰርና ሲፈታ ከነበረው ጋዜጠኛ Continue Reading

ይህቺ ሱዳናዊት ሳማንታ ፓወር፣ ሊንዳ ቶማስና ማርክ ሎውኮክን ከፊት አሰልፋ ” በአስቸኳይ እርዳታ” ስም ኢትዮጵያ ላይ ዘመቻ ስታካሂድ ዋናው ዓላማ በቀጣይ የጂሰባት አገሮች ስብሰባ ላይ ኢትዮጵያን አንገቷን የሚቀነጥስ ውሳኔ እነዲወሰን ጫና ላምሳደር ነበር። የሆነው ግን የተገላቢጦሽ ነው። አቶ ጥበቡ እንዳሉት ኢትዮጵያ ክፉውን ጊዜ ያለፈች ይመስላል።

የዘወትር ተባባሪያችን የአውሮፓው ዲፕሎማት እንዳሉት ” ዲፕሎማሲው ላይ በጥብቅ እየተሰራ ነው። ሁሉም ጉዳይ መልክ ይይዛል” ሲሉ የጂ ሰባት አገሮችን ውሳኔ ለስላሳና የሴራው አምራቾች ከጠበቁት በታች የሆነ እንደሆነ አመልክተዋል። ግን ደረት አያስነፋም።

READ ALSO THIS የG-7 ሀገራት መግለጫ ስለኢትዮጵያ ምን አለ?

በእንግሊዝ እየተካሄደ ያለው የቡድን 7 ሃገራት ስብስባ ዛሬ መግለጫ አውጥቷል:: በመግለጫው የኢትዮጵያ ጉዳይም ተካቷል:: በአንቀፅ 54 ላይ የሰፈረው መግለጭ ቃል በቃል የሚከተለውን ይላል። ትርጉም 54. “በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ውስጥ እየተካሄደ ባለው ግጭት እና እየወጡ ባሉ ሪፖርቶች ምናልባት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በረሃብ ሁኔታ ውስጥ ሊሆኑ ስለሚችሉ የሰብአዊ አደጋዎች በጣም ያሳስበናል፡፡ የጾታ ጥቃትን ጨምሮ እየተፈፀሙ ያሉContinue Reading

በስብሰባው ላይ ጫና ለማሳደር ሚዲያዎች ያራገቡትን የሴራ ዘመቻ ለመመከት ከአውሮፓ አገራትና ቁልፍ ወዳጅ ከሆኑ ክፍሎች ጋር ሰፊ ውይይት፣ መካሄዱን መንግስትም ይፋ እንዳደረገው ባልስልጣናቱ የጠቅላይ ሚኒስትር አብይን መልዕክት በመያዝ ባካሄዱት የፊት ለፊት ንግግር ከፍተኛ ለውጥ መታየቱን ዲፕሎማቱ አስታውቀዋል። ከሁሉም በላይ ግን ኢትዮጵያዊያን የፈጠሩት አንድነትና ያለመታከት ያካሄዱት ዘመቻ ታላቅ ክብር የሚሰጠው እንደሆነ ገልጸዋል።

አቶ ጥበቡ ለኢትዮ 12 በላኩት መልዕክት “በቃ ይሄው ነው። ማለት ያለባቸውን ብለዋል። ያሉት ሁሉ ከቀድሞው የለዘበ እና ከተጠበቀው አንፃር ኢምንት ነው” ብለዋል። የአማራ ሚሊሻ የኢትዮጵያ ሰራዊት ወዘተ የሚሉ አልስፈለጊ ጉዳዮችን ጭራሽ አለማንሳታቸው በዛኛው ጎራ ለቆሙት ሽንፈት እንደሆነ ጠቅሰዋል።
” ማዕቀብም ሆነ ማስጠንቀቂያ የለውም።ያሳስበናል ያሉትን ሃሳብ ነው ያቀረቡት።ያወገዝነውን ነው ያወገዙት። መፍትሄ ያሉትን ጥሪ ነው አቅርበዋል” ያሉት አቶ ጥበቡ፣ ለዚህም ቢሆን መንግስት የተደራጀና አጥጋቢ ምላሽ መስጠት ብቻ እንደሚጠበቅበት ነው ያመለከቱት።


እንደ ዲፕሎማቱ ሁሉ አቶ ጥበቡም ዲፕሎማሲው ላይ በጥብቅ ከተሰራ ሁሉም ነገር የሚለወጥ ስለመሆኑ የጂ ሰባት አገሮች የአሁኑ ውሳኔ ምልክት እንደሆነ ገልጸዋል። መልዕታቸውን ሲያተቃልሉም “ክፉው ጊዜ በእርግጥም አልፏል፤ ዛሬ የኢትዮጵያ ልጆች ከሰሞኑ ጭንቀት እፎይ ብለዋል፤ መንግስት ይህን እድል ይጠቀምበት፤እስከ መጨረሻው ሁኔታውን ይቀይረው፤ ኢትዮጵያዊያንም ህብረታችንን እናጠናክር” ብለዋል።
.
በሌላ በኩል የሚሰጡ ጥቅል አስተያየቶች “በጠላትነት የያዙን የዩኤስአይዲ ሳማንታ ፓወር፣ ሊንዳ ቶማስ ፣ እንግሊዛዊው የተባበሩት መንግስታታ የሰብአዊ እርዳታ ዘርፍ ሃላፊ እንግሊዛዊ ሰር ማርክ ሎውኮክ ሃዘን ተቀምጠዋል” የሚሉ አስተያቶች እየተሰሙ ነው። አንዳንዶች ደግም “እነ ማርቲን ፕላውት ቴድሮስ አድሃኖም እና ሌሎቹ ቡድንተኞች በሙሉ ልባቸው ወድቋል” ብለዋል። ሁሉም የጠበቁት ስላልሆነላቸው “ጥልቅ ሃዘን ላይ ናቸው” ሲሉም የሳፉ አሉ።

ሰሞኑን ሳማንታ ፓወር እና ሊንዳ ቶማስ ተራ አክቲቪስት ሆነው Tigrai can’t wait ማለት ሁሉ ጀምረው እንደ ነበር ያወሱ ” ኢትዮጵያ ተረፈች” ሲሉ አፊዘውባቸዋል። ከመግለጫው በኃላ ግን ሳማንታ ፓወር የትግራይን ጉዳይ ትታ ስለ ሆንድራንስ ስለ ጓቲማላ ስለ ኤልሳልቫዶር መፃፍ መጀመራቸውን ጠቅሰው ያሽሟተጡም አሉ።

“የኢትዮጵያ ጠላቶች ልባቸው ወደቀ” ብል ጀምሮ “የጁንታው የቱዊተር ታጋዬችም ረሃብ ማለት እንዳላዋጣቸው ስላወቁ ማርቲን ፕላውት የጀመረውን ዘመቻ “ኢትዮጵያ የኬሚካል ጦር መሳሪያ ወደ ትግራይ አጓጉዛለች በማለት ከበሮ እየመቱ ነው” ያለው ሳለሁልህ አየለ ነው። ሳሳሁልህ “ገንዘባቸውን በሎቢስት እየጨረሱ ስለሆነ እኛም፣ ኢትዮጵያም፣ የትግራይ ሕዝብም በቅርቡ ያርፋል። ምክንያቱም ተስፋቸው በቡድን ሰባት ሃገራት መግለጫ አርቀው ቀብረውታልና! በኢትዮጵያ ስም ተሹሞ ኢትዮጵያን እያረደ ያለው ቴዎድሮስ አድሃኖምም መጽናናት ይሁንለት” ሲል አስተያየቱን ያጠቃልላል።

በጂ ሰባት አገራት ውሳኔ ኢትዮጵያ የማትስማማበት ጉዳይ አንድና አንድ ብቻ ነው። እሱም ከትህነግ ትርፍራፊ ሃይል ጋር መደራደር። ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም ከፍተኛ የሎቢ ስራ መሰራቱን በመጥቀስ ከፍተና ድል እንደሚመዘገብ በስራቸው ላሉ መናገራቸውን አካታን ረሃብን የትግል መሳሪያ በማድረግ የተካነው ትህነግ ድርድርን በረሃብ ጫና ለማምጣት እየሰራ ያለውን ሪፖርት እናቀርባለን።


 

Exit mobile version