የራያ አዘቦ ህዝብ በአሸባሪው ሕወሃት ዋጋ እየከፈለ መሆኑን የራያ ራዩማ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ አስታወቀ።የአገር መከላከያ ሰራዊት ትግራይን ለቆ ከወጣ ጀምሮ የራያ አዘቦ ተወላጆች የሆኑ በርካታ ሰዎች መገደላቸውንም ፓርቲው አስታውቋል።
በተጨማሪም ከ30 ሺህ በላይ ከአካባቢያቸው ተሰደዋል።የራያ ራዩማ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የወጣቶች ዘርፍ ሃላፊ አቶ ጥጋቡ ጎበና እና በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የራያ አዘቦ መኾኒ ከንቲባ አቶ አለ በርዎ ከኢዜአ ጋር በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ውይይት አድርገዋል።የራያ አዘቦ ህዝብ ባለፉት ሶስት ዓመታት አገራዊ ለውጡን ተቀብሎ የህዝቡን ጥያቄ በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ሲሰራ እንደነበር አስታውሰዋል።
ህዝቡ በአሸባሪው ሕወሃት ከማንም በላይ ጭቆና ሲደረስበት እንደነበር አስታውሰው፤ ክልሉን መከላከያ ከያዘው ጀምሮ በተለይ አርሶ አደሩ ተረጋግቶ ወደ እርሻው መግባቱን ተናግረዋል።ሆኖም በአሁኑ ወቅት መንግስት በትግራይ ክልል የወሰደውን የተናጠል ተኩስ አቁም ውሳኔ ተከትሎ ህዝቡ በአሸባሪው ሕወሃት ዋጋ እየከፈለ መሆኑን ገልጸዋል።
የትግራይ አርሶ አደር ተረጋግቶ የእርሻ ስራውን እንዲያከናውንና ሰብዓዊ ድጋፍ እንዲደርስ መንግስት ያደረገው መልካም ተግባር የራያ አዘቦ ህዝብ በአሸባሪው ሕወሃት ግድያና ሰቆቃ እየደረሰበት መሆኑን ጠቁመዋል።
ክልሉ በመከላከያ ቁጥጥር ስር እያለ የራያ አዘቦ አርሶ አደር ተረጋግቶ የእርሻ ስራውን ሲሰራ እንደነበር አስታውሰው፤ “አሁን ከአካባቢው መልቀቁን ተከትሎ ችግር ውስጥ በመግባቱ መፍትሄ ያስፈልገዋል” ብለዋል። የራያ አዞቦ ህዝብ ከዚህ የከፋ ጉዳት ከማስተናገዱ በፊት መንግስትና መከላከያ እንዲደርስለትም መጠየቁን ኢዜአ ዘግቧል።
- ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናውቤት የተባለች አንዲት ሴት እንዲህ ብላለች፦ “ደም ማነስ የያዘኝ በአሥራዎቹ ዕድሜ ሳለሁ ነው። ቶሎ ይደክመኝ፣ አጥንቶቼን ይቆረጥመኝ፣ እንዲሁም ትኩረቴ… Read more: ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናው
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ ወገኖች አስታውቀዋል። ጎን… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ። ለውጭ አገር ሚዲያዎች… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት
- የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡምየፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የትራንስፖርት ስምሪትና የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር ሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ 11 ግለሰቦች በስር ፍ/ቤት የተሰጠውን ዋስትና አፀና።… Read more: የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡም
- መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለየአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ ምክንያቱም “የኢትዮጵያ መንግሥት በሕገ ወጥ መንገድ የአውሮፓ ኅብረት አገራት ውስጥ የሚኖሩ… Read more: መንግስት ስድተኞችን አልቀበልም በማለቱ የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጊዜያዊ የቪዛ ገደብ ጣለ