Site icon ETHIO12.COM

መፍትሔው የአባቶቻችን መንገድ መከተል ነው!(ረዘም ያለ የድርጊት ማመላከቻ)


የአማራ ሕዝብ ደመኛ ጠላት የሆነው ትህነግ በወታደራዊ ድል ተሸንፎ፣ ተዋጊው ተበትኖ፣ አመራሩ ህይዎቱን ለማትረፍ ሲቅበዘበዝበት ከነበረበት ነባራዊ ሁኔታ ወጥቶ እንደገና እንዲሰባሰብ፣ ወታደር እንዲመለምልና እንዲያሰለጥን፣ በየቦታው የቀበረውን መሳሪያ አውጥቶ እንዲታጠቅና የትግሬን ህዝብ ከሊቅ እስከ ደቂቅ አደራጅቶ አማራን እንዲወርና እልቂት እንዲፈጽም መንገዱ ተከፍቶለት እየተግተለተለ ነው።

በዚህ ሂደት ውስጥ የአገሪቱ የፓለቲካና ወታደራዊ መሪዎች ወይም ከፍተኛ ወታደራዊና ፓለቲካዊ አመራሮች ወይ ከፍተኛ የአመራር ድክመት አሳይተው ለዚህ ሁናቴ ዳርገውናል፤ አልያም ደግሞ በታቀደና በተጠና መንገድ የአለም አቀፉን ማህበረሰብ ለመደለል ሲባል የፓለቲካዊ ውሳኔ ተወስኖ ወልቃይትና ራያን ለትህነግ ዳግም ቅኝ ግዛት ለመመለስ ከመጋረጃ ጀርባ ስምምነት ተፈጽሞ ሊሆን ይችላል። የፌደራል መንግስትም ሆነ የወታደራዊ፣ የጸጽታና ደህንነት ተቋማት ይሄን ጉዳይ በተመለከተ ሀላፊነት በተሞላበት መንገድ መግለጫ እንኳን አልሰጡም።

የተፈፀመው የፓለቲካ ሴራም ይሁን የአመራር ድክመት ትህነግ ወደራያና ወልቃይት፣ ጠገዴ ጠለምት የሚያደርገው እንቅስቃሴ እስከ አላማጣና ማይ–ጠምሪ እስክትድረስ ድረስ የአገር መከላከያ ሰራዊት ምንም አይነት የመከላከልና መልሶ የማጥቃት ርምጃ ካለመውሰዱም በላይ በሁለቱም ግንባሮች የአማራ ልዩ ሀይልና ሚሊሻ ወደኋላ እንዲያፈገፍግ እንደተደረገ ከአካባቢው የሚወጡ ሪፓርቶች አመላክተዋል።

በዚህም ሆነ በዚያ የትህነግን ፋሽስታዊ ወረራና የትግሬን ወደ አማራ ርስቶች እያደረገ ያለውን መስፋፋት የመከላከልና የመመከት ሸክም ለጊዜውም ቢሆን በአማራ ህዝብ ላይ ወድቋል። የአማራ ክልል መንግስት «የህልውና ዘመቻ» ብሎ በሰየመው ጥሪ ሚሊሻና ልዩ ሀይሉን ያንቀሳቀሰ ሲሆን፣ የሀብትና የቁሳቁስ ማሰባሰብ ዘመቻም ጀምሯል።

የአማራ የፓለቲካ ድርጅቶችም ለህዝባቸው ታሪካዊ የክተት ጥሪ አስተላልፈዋል። ስለዚህ በመላው ኢትዮጵያ የሚኖረው የአማራ ህዝብ ከሊቅ እስከ ደቂቅ የሚከተሉትን የተግባር እንቅስቃሴ ያለአንዳች መዘግየትና ማመንታት መፈጸም ይገባዋል፦

1) በመጀመሪያ ወጣቱ በየአካባቢው የቀበሌና የወረዳ መስተዳድሮች እንዲያደራጁትና ወደ ሰሜን አማራ በተደራጀ መንገድ ለመዝመት አጭር ስልጠና እንዲሰጡትና እንዲያዘምቱት መጠየቅ አለበት። ስልጠናው ያለአንዳች መጓተት በአስቸኳይ በየቀበሌው መሰጠት አለበት።

የግል ትጥቅ ያለው የራሱን ትጥቅና ስንቅ አዘጋጅቶ በመያዝ መዘጋጀት፣ የግል ትጥቅ የሌለው ደግሞ ከአካባቢው መስተዳድር መጠየቅ፤ በዚህ ሂደት ትጥቅ ማግኜት ያልቻለ ደግሞ እንደ ገጀራ፣ ጩቤ፣ ሳንጃ፣ ጊሌ፣ ቆንጨራ፣ ጦርና ሌሎች የባህልና በአካባቢው የሚያገኛቸውና በቀላሉ ሊያሰራቸው የሚችሉ የነፍስ ወከፍ የጨበጣ መሳሪያዎችን አዘጋጅቶ፣ የጦር መሳሪያ ካለው ጓደኛና ወዳጅ ዘመድ ጋር ራሱን አደራጅቶ ወደ ሰሜን ለመዝመት መዘጋጀት አለበት። መሳሪያ ያለውና ለመዝመት የማይችል ግለሰብ ካለ በአካባቢው መዝመት ለሚችሉ ወጣቶች መሳሪያውን በውሰት መስጠት አለበት።

መሳሪያ የሌለው ለዘማቾች የአቅሙን ስንቅና አልባሳት አዘጋጅቶ መስጠት አለበት። የአካባቢ ጀግኖችን መሪና የጎበዝ አለቃ አድርጎ መሰየምና በየአካባቢው በየደረጃው የሚመሩ የእዝ ሰንሰለቶች ያሉት የህዝባዊ ሰራዊት/የአርበኛ ጦር ማዘጋጀትና መዘጋጀት ያስፈልጋል።

አሁን በየወረዳው ካለው ወጣት የህዝብ ቁጥር አንፃር ከእያንዳንዱ ወረዳ ቢያንስ ከ500 እስከ 1000 ወጣትና ጎልማሳ መልምሎ ማዘጋጀት ይቻላል። በትንሹ ከአማራ ክልል ብቻ ከ100 ሺ እስከ 150 ሺህ ህዝባዊ ሰራዊት መመልመል፣ የአጭር ጊዜ ወታደራዊ ስልጠና መስጠትና ለአርበኝነት ትግል ማዘጋጀት ይቻላል።

ይህን ሀይል ስልጠናውን ካጠናቀቀ በኋላ ከልዩ ሀይሉና ሚሊሻው ጋር አደራጅቶ የአማራን ህዝብ ህልውና ማስከበር ይቻላል። አዲስ አበባን ጨምሮ ከክልሉ ውጪ የሚኖረው በሚሊየን የሚቆጠር የአማራ ወጣትም በተደራጀ መንገድ ወደ አማራ ክልል በመጓዝ የህልውና ትግሉ አካል ሊሆንና ሊቀላቀል ይገባል።

2) የአካባቢ መስተዳድሮች ከተለያዩ የፓለቲካና የማህበረሰብ አደረጃጀቶች ጋር በመቀናጀት ወጣቱን የመመልመል፣ የማደራጀትና በተገኘው ትጥቅና ስንቅ እንዲዘጋጅ በማድረግ በአካባቢው ከሚገኘው ማህበረሰብ ሀብት በማሰባሰብና ተሽከርካሪ በመመደብ ለግዳጅ ዝግጁ እንዲሆኑ ማድረግ ስራን በተቀናጀ መንገድ መከወን ያስፈልጋል።

3) በየደረጃው ለአማራ ህዝብና ለኢትዮጵያ እየታገላችሁ ያላችሁ የፓለቲካ ፓርቲ አመራሮችና አባላት በሙሉ ደግሞ ልክ የትግሬ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ከገዢው ትህነግ ጋር የነበራቸውን ልዮነት ለጊዜው ወደ ጎን አድርገው አብረው እንደተሰለፉት ሁሉ ከአማራ ክልል ከገዢ ፓርቲ ጋር ያለንን ግንኙነት ወደጎን በመተው በየደረጃው ከሚገኙ የአማራ ብልጽግና አመራሮች ጋር ተባብሮ በመቆምና መላ ህዝባችን በማስተባበር ህልውናውን እንዲያስከብር ተቀናጅተን መስራትና ህዝባችን የገጠመውን የህልውና አደጋ እስኪከበር ድረስ ልዩነታችን በይደር ይዘን በትብብር ህዝባችን ለማዳን መነሳት አለብን።

የአብን አመራርና አባላት ድርጅታችን ባቀረበልን ጥሪ መሰረት ከነገ ጀምሮ ከቀበሌ፣ ከወረዳና ከተማ አስተዳደሮች የመንግስት መስተዳድር ሀላፊዎች ጋር በመቀናጀት ሀላፊነታችንን መወጣት አለብን።

4) የዞንና የክልሉ መስተዳድሮች በተመሳሳይ መንገድ ከየቀበሌውና ከየወረዳው የተደራጀውን ሀይል ስምሪት ለመስጠት ከልዩ ሀይሉና ከሚሊሻው ጋር በደጀንነትና ጎን ለጎን ሆኖ እንዲዋጋ ለማድረግ በሚያሰችል መልኩ ማዘጋጀት፣ ህዝቡን ከጫፍ ጫፍ በአጭር ጊዜ በማነቃነቅ ህልውናውን እንዲያስከብር ማድረግ ያስፈልጋል።

5) የአማራ የሀይማኖት መሪዎች፣ ሽማግሌዎችና የተለያዪ የሲቪክ አደረጃጀቶችም ህዝቡን በመቀስቀስና በማንቀሳቀስ ነፃነቱን እንዲያስከብር የሚጠበቅባችሁን በመወጣት፣ የምትችሉም ግንባር ድረስ በመዝመት ለነፃነታችሁ ሰማዕት ለመሆን መዘጋጀት ያስፈልጋል።

6) የከተማ ከንቲባዎችና የወረዳ አስተዳደሮች ከማህበረሰቡ ለዘመቻው የሚሆን ሀብት ከማሰባሰብ በተጨማሪ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሊከናወኑ የሚችሉ የሀብት ማሰባሰቢያ ዘዴዎችን በመጠቀም ከህዝባችን በአንድ ጊዜ በቢሊየን ብሮች የሚደርስ ገንዘብ ማሰባሰብ እንደሚቻል በመገንዘብ ወደስራ መግባት አለባችሁ።

ለምሳሌ፦ 15ቱ የዞንና ሜትሮፓሊቲያን ከተሞች 50 ቦታዎች በአንድ ጊዜ መቶ ፐርሰንት ክፍያ የሚፈፀም የሊዝ ጨረታ ቢያዘጋጁና አሁን ባለው አማካይ የሊዝ ዋጋ ቢሸጡ፦ 15×50×1,500,000 ወደ 1 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር መሰብሰብ ይችላሉ። በተመሳሳይ ከ140 አካባቢ ወረዳ ከተሞችና ንዑስ ከተሞች እያንዳንዳቸው 50 ቦታዎች በ500 ሺህ ብር ሊዝ ቢሸጥ ወደ 14050500,000 = 3.5 ቢሊየን ብር መሰብሰብ ይቻላል። በጥቅሉ በጥቂት ቀናት ውስጥ ወዲያውኑ ካሽ መክፈል ለሚችሉ ሰዎች ቦታውን በማስተላለፍ ከ5 ቢሊየን ብር በላይ የሆነ ገንዘብ ማሰባሰብ ይቻላል። በተጨማሪም ከክልሉ መንግስትና ከልማት ድርጅቶች ተጨማሪ በጀት ማሰባሰብ ይቻላል።

7) ከዚህ በፊት በተለያየ ጊዜ ከጦር የተቀነሱ የአማራ የጦር መኮንኖችን፣ መስመራዊ መኮንኖችንና ባለሌላ ማዕረግተኛ ወታደራዊ አዛዦችን ወደ አማራ ልዩ ሀይል፣ ሚሊሻና ህዝባዊ ሀይል እንዲመለሱ በቀረበው ጥሪ መሰረት እያንዳንዱ የአማራ ወታደራዊ አመራርና ተመላሽ ሰራዊት የክልሉን መንግስት ጥሪ በቀናነት ተመልክቶ መመለስና ህዝባዊ ሀይሉን ወደመምራት መምጣትና ህዝባችን ከፈጽሞ ጥፋት መታደግ የሚገባን ጊዜ ላይ መድረሱን መረዳት ያስፈልጋል።

8) የአማራው ዳያስፖራ በተደራጀና እና በተቀናጀ መንገድ የፋይናንስ፣ የአድቮኬሲና የውጭ ግንኙነት ስራዎችን መስራትና የአገር ቤቱን ትግል ማገዝ ይችላል። እያንዳንዱ የአማራ ዳያስፓራ በየአካባቢው የአማራ ኮሚኒቲዎችን በመቀላቀልና በቋሚነት በወር በአማካይ $100 ማዋጣት ይችላል። 10 ሺ የአማራ ዳያስፖራ እንኳ ይህን ማድረግ ቢችል በወር 1000000 ሚሊየን ዶላር ማበርከት ይችላል። በዚህም ለትግሉ አስፈላጊ የሆኑ እንደ ሳታላይት ስልኮችና የህክምና ቁሳቁሶች ለታጋዩ ወገናቸው ማድረስ ይችላሉ።

9) የአማራ ባለሀብቶች ካላቸው ገንዘብ ጥቂቱን እንኳ ለህልውና ትግሉ እንዲሰጡ ማሳመንና ማግባባት ያስፈልጋል።

10) የአማራ ሴቶች የሚችሉ መዝመት፣ መዝመት የማይችሉት ደግሞ የኋላ ደጀን በመሆን ስንቅ ማዘጋጀት፣ ስንቅ በማቅረብ፣ የደከመውን በማበረታትና የቆሰለውን በማከም ከወንዶች እኩል ለህልውና ትግሉ ግዴታቸውን ለመወጣት ከአሁኑ ጀምሮ ዝግጅት ማድረግ አለባቸው።

11) የማህበራዊ ሚዲያ አክቲቪስቱ በዚህ ሰአት የአማራን ህዝብ የሚከፋፍል፣ የክልሉን መሪዎች ከነድከመታቸውም ተቀብሎ ከጎናቸው ሆኖ ከማገዝና የአማራን ህልውና ለማስከበር ከመዘጋጀት በዘለለ በምንም አይነት መንገድ እጣት መቀሳሰር፣ መውቀስ፣ መስደብ፣ ማንቋሸሽ፣ የጎሪጥ መተያየት ወዘተ እንደማያዋጣ ተገንዝቦ፣ ተባብረን መቆም አማራጭ የሌለው መሆኑን በመረዳት በሀላፊነት መንቀሳቀስ ይጠበቅብናል።

12) በአገር ውስጥና በውጭ አገራት የተለያዩ ተቋማት ያላችሁ ፊደል የቆጠራችሁ የአማራ ልጆችም በህልውና ትግሉ በቀጥታ ከመሳተፍ በተጨማሪ እንደ ትዊተር ያሉ ተጽዕኖ ፈጣሪ ማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎችን በመጠቀም፣ እንዲሁም የአለም አቀፍ ሚዲያና ተቋማትን ያለመሰልቸት በማስረዳትና በመጎትጎት ለህዝባችን በተናበበ ዘመቻ መልክ ድምጽ የምትሆኑበት ጊዜው አሁን ነው።

13) ከፌደራል መንግስቱም ጋር ግልጽ ዘለፋና ፍጥጫ ውስጥ ከመግባትና ያማያስፈልግ መጓተት ውስጥ ከመጠለፍ ይልቅ የህልውና ትግላችን እያካሄድን ጎን ለጎን ደግሞ ፌደራል መንግስቱ አገርን ከአሸባሪዎች የመጠበቅ ሀላፊነቱን እንዲወጣ ጫና የማድረግ ስራ እንስራ። ፌደራል መንግስቱ ይህን ማድረግ ባይችል እንኳ በአማራ ህዝብ ላይ ግልጽ ትንኮሳና ጣልቃ ገብነት እስካልተፈመ ድረስ ከፌደራል የፀጥታ አካላት ጋር ግጭት ውስጥ ላለመግባት መጠንቀቅ ያስፈልጋል።

ማጠቃለያ፦

የአማራ ህዝብ ስማ፣ እንደ አባቶችህ የአርበኝነት ታሪክ የምትጽፍበት የመጨረሻው ደወል ተደውሏል! አንድም አማራ ሳትቀር ተነስ፣ ለህልውናህ እስከመጨረሻው ታገል፣ ህልውናህን በክንድህ አስከብር!

አማራ በጠንካራ ክንዱ ህልውናውን ያስከብራል!

Exit mobile version