ሀምሌ 10/2013 (ኢዜአ) ጨፌ ኦሮሚያ በክልሉ የፍትህ ተደራሽነትና ትክክለኝነትን ለማረጋገጥ ያግዛል ላለው የባህላዊ ፍርድ ቤቶች ምስረታ እውቅና የሚሰጥ አዋጅ አጸደቀ።
ጨፌው የ2014 የክልሉ በጀት 124 ቢሊዮን ብር እንዲሆን አጽድቋል።
ጨፌ ኦሮሚያ እያካሄደው የሚገኘው 14ኛ መደበኛ ጉባኤ በሁለተኛ ቀኑ የባህላዊ ፍርድ ቤቶች ምስረታ እውቅና የሚሰጥ አዋጅን ማጽደቅን ጨምሮ የተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቷል። ባህላዊ ፍርድ ቤቶቹ ከቀበሌ ጀምሮ የሚመሰረትና የክልሉ ሕዝብ በቀደመው ባህሉና ወጉ መሰረት ፍትህ እንዲያገኝ ያግዛል ነው ተብሏል።
ፍርድ ቤቶቹ በተለይ በመደበኛ ፍርድ ቤቶች በፍትህ አሰጣጥ ሂደቱ ላይ ፈተና የሆነውን ሀሰተኛ ምስክርነት ለመቀነስ እንደሚረዳም ተገልጿል። በዋናነት የክልሉ ሕዝብ የቀደመ ባህላዊ የፍትህ አሰጣጥ ሂደትን ተከትሎ የሚያጋጥሙ አለመግባባቶችን ለመፍታት ያስችላልም ተብሏል።
ረቂቅ አዋጁን ያቀረቡት የህግ ተመራማሪው አቶ ሚልኪ መኩሪያ እንደሚሉት ፍርድ ቤቶቹ የፍትህ ተዳራሽነትን የበለጠ ያጠናክራሉ። ከዚህ በፊት በአብዛኛው የክልሉ ነዋሪዎች ፍትህ ለማግኘት ረጅም ጉዞ በማድረግ ለአላስፈላጊ ወጪ ይዳረጉ ነበር ነው ያሉት።
በአዋጁ መሰረት የሚቋቋሙ ፍርድ ቤቶች የክልሉ ሕዝብ ፍትህን በቅርበትና በእውነት ላይ ተመስርቶ እንዲያገኝ ይረዳዋል ብለዋል። ፍርድ ቤቶቹ የመጀመሪያና በፍርድ ሂደቱ ያልረካው አካል አቤት የሚለበት ሁለተኛ እርከን ፍርድ ቤት እንዲኖረው ሆኖ እንደሚደራጅም ገልጸዋል።
ከዚህ ባለፈ ባህላዊ ፍርድ ቤቶቹ አምስት አባላት ያሉትና አባላቱም ለስምንት አመታት የሚያገለግሉ እንደሚሆኑ ተናግረዋል። እነዚህ ፍርድ ቤቶች ከመደበኛና ከማህበራዊ ፍርድ ቤቶች ጎን ለጎን የሚሰሩ ሲሆን ለክልሉ ህዝብ ትልቅ ጥቅም የሚሰጡ እንደሆነም ገልጸዋል።
በዚሁ መሰረት አዋጁ በጨፌው አባላት በሙሉ ድምጽ ጸድቋል። በተመሳሳይ ጨፌው የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት አዳምጦ ከተወያየበት በኋላ ሪፖርቱን በሙሉ ድምጽ አጽድቆታል።
በተጨማሪም ምክር ቤቱ የኦሮሚያ ክልል የአስር ዓመት እቅድ ላይ ሰፊ ውይይት አድርጎ እቅዱን አጽድቆታል። በመጨረሻም የጨፌ ኦሮሚያ ምክር ቤት የክልሉን ኦዲተር ጀነራል እቅድ አፈጻጸም፣ የ2013 ዓ.ም ተጨማሪ በጀት እንዲሁም የ2014 ዓ.ም በጀት ላይ ውይይት በማድረግ አጽድቆታል።
በዚህም የክልሉ የ2014 በጀት 124 ቢሊዮን ብር ለካፒታልና ለተለያዩ ወጪዎች እንዲውል አጽድቋል። በጀቱ 19 ቢሊዮን ብር ለተለያዩ ወጪዎች፣ 29 ቢሊዮን ለካፒታል በጀትና 73 ቢሊዮን ብር ለወረዳዎችና ለከተማ አስተዳደሮች ድጋፍ እንዲሁም 600 ሚሊዮን ብር ለተጠባባቂ በጀት ተይዟል።
- የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ“ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ” እያሉ በስሟ ሲምሉ የነበሩ ብዙዎች ነበሩ፤ ከልባቸው ለቃላቸው ታምነው ልጅ የሆኗት ግን ጥቂቶች ብቻ ናቸው። አንዳንዶች በስሟ የሚገዘቱት እንጀራዋን ለመብላት እንጂ መከራዋን… Read more: የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ
- አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ“ወገኖቼ እንማርና እናስተምር፣ ወንጀልን እንጸየፈው፣ እንጥላው፣ ወንጀልን ተጸይፈን ወንጌልን እንውደደው፣ በወንጌል እንኑር፣ ወንጌል ሕጓም ስርዓቷም ያማረች ናት፤ ወንጌላዊ መኾን መልካም ነው፣ ወንጀለኛ መኾን ግን… Read more: አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ
- ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናውቤት የተባለች አንዲት ሴት እንዲህ ብላለች፦ “ደም ማነስ የያዘኝ በአሥራዎቹ ዕድሜ ሳለሁ ነው። ቶሎ ይደክመኝ፣ አጥንቶቼን ይቆረጥመኝ፣ እንዲሁም ትኩረቴ በቀላሉ ይከፋፈል ነበር። ሐኪሜ የብረት… Read more: ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናው
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ ወገኖች አስታውቀዋል። ጎን ለጎን የትግራይ ከፍተኛ ባለስልጣናትና የዞን… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ። ለውጭ አገር ሚዲያዎች ዜና የሚያቀብሉና እነሱኑ የሚከተሉ ስምምነቱ… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት
- የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡምየፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የትራንስፖርት ስምሪትና የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር ሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ 11 ግለሰቦች በስር ፍ/ቤት የተሰጠውን ዋስትና አፀና። ፍርድ ቤቱ ተጠርጣሪዎቹ ከሀገር እንዳይወጡ… Read more: የነዳጅ ድጎማን በማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለተጠረጠሩ በስር ፍ/ቤት የተሰጠ ዋስትና ፀናላቸው፤ ከአገር አይወጡም