“አሸባሪ” የሚል መዕረግ ተሸልሞ ወደ መቀለ የተመለሰው የትህነግ ቡድን ” ፈሪና ጀግና” በሚል እተፈራረጁ መሆኑንን በአሜሪካ የድርጅቱ ዋና ደጋፊ መናገራቸው ተሰማ። በረሃ የወረዱት ” ጅግና” ሲባሉ፤ ከተማ ተደብቀው የነበሩ ” ፈሪ” እየተባሉ ነው።
ትህነግ ከበረሃ ወጥቶ ወደ መቀለ ሲገባ ከተደበቁበት ከወጡት መካከል ዳንዔል ብርሃኔ ይገኝበታል። የድርጅቱ ዋና ደጋፊ እንዳሉት እነ ዳንኤል የሳተላይት ስልክ እንዳይጠቀሙ ተከልክለዋል። ለዚህም ምክንያቱ ” ፈሪ” በመሆናቸው ነው።
ለወትሮው ከማህበራዊ ገጽ የማይጠፋውና ወደ መቀለ ከሄደ በሁዋላ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይን በመስደብ፣ በማሽሟጠጥና በማውገዝ ስራ ተሰማርቶ የነበረው ዳንዔል፣ መንግስት እንዴት እንደሚቀየር፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዴት የዓለሙ የጦር ወንጀለኞች ፍርድ ቤት እንዴት እንደሚቀርቡ፣ ጦርነቱ ከሁለት ሳምንት በላይ እንደማይፈጅ በተደጋጋሚ በማስረዳት ቀዳሚ ነበር።
ተደብቆ ሕይወቱን ያተረፈው ዳንዔል ስልክ ፈልጎ ማጣቱን ከላይ የተገለጹት የትህነግ ዋና አባል በስሞታ ደረጃ ከሌሎች መስማታቸውን አስታውቀዋል። ቀደ ባለው ጊዜ ዳኒ የጌታቸው አሰፋ ወገን እንደነበር በተደጋጋሚ ሲነገር ነበር። “የደህንነቱ ሹም አለመኖራቸው ዳኒ ስልክና ኢንተርኔት ብርቁ ሆነ” ሲል የሰማውን ወሬ ያጋራን የአሜሪካ ተባባሪያችን ነው።
እንደ ዳኒ ሁሉ በርካታ የተደበቁ የነበሩ ” ፈሪ” ተብለው ፊት እንደተነሱ ከመቀለ መረጃ ያላቸው አስታውቀዋል።
- የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ“ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ” እያሉ በስሟ ሲምሉ የነበሩ ብዙዎች ነበሩ፤ ከልባቸው ለቃላቸው ታምነው ልጅ የሆኗት ግን ጥቂቶች ብቻ ናቸው። አንዳንዶች በስሟ የሚገዘቱት እንጀራዋን ለመብላት… Read more: የኢትዮጵያን – “መከራዋን ካልተሸከምንላት ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው” አብይ አሕመድ
- አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ“ወገኖቼ እንማርና እናስተምር፣ ወንጀልን እንጸየፈው፣ እንጥላው፣ ወንጀልን ተጸይፈን ወንጌልን እንውደደው፣ በወንጌል እንኑር፣ ወንጌል ሕጓም ስርዓቷም ያማረች ናት፤ ወንጌላዊ መኾን መልካም ነው፣ ወንጀለኛ… Read more: አቡነ አብርሃም “እንዳይረፍድብን” ሲሉ ለመጸጸት እንኳን ዕድል እንዳይታጣ አስጠነቀቁ
- ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናውቤት የተባለች አንዲት ሴት እንዲህ ብላለች፦ “ደም ማነስ የያዘኝ በአሥራዎቹ ዕድሜ ሳለሁ ነው። ቶሎ ይደክመኝ፣ አጥንቶቼን ይቆረጥመኝ፣ እንዲሁም ትኩረቴ በቀላሉ ይከፋፈል ነበር።… Read more: ደም ማነስ—መንስኤው፣ ምልክቶቹና ሕክምናው
- የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?ሰሞኑን በራያ አላማጣ አቅጣጫ የትግራይ የታጠቁ ሃይሎች በግጭት መሰማራታቸውን ተከትሎ ከሃምሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ገለልተኛ ወገኖች አስታውቀዋል። ጎን ለጎን የትግራይ ከፍተኛ… Read more: የትግራይ አመራሮች ከፌደራል መንግስት ጋር ያደረጉት የተለየ ስምምነት አለ?
- ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረትዜናው ከተሰማ ጀምሮ በከፍተኛ የተቃውሞ መግለጫና ማስተንቀቂያ የታጀበው የኢትዮጵያና የሶማሌላንድ ስምምነት ወደ መገባደዱ እያመራ እንደሆነ ተገለጸ። ለውጭ አገር ሚዲያዎች ዜና የሚያቀብሉና እነሱኑ… Read more: ሶማሌላንድ የባህር በር ስምምነቱ በሁለት ወር ውስጥ ይቋጫል አለች፤ “መንግስት ውሉን ትቶታል” አቶ ኤሊያ መሰረት