“አሸባሪ” የሚል መዕረግ ተሸልሞ ወደ መቀለ የተመለሰው የትህነግ ቡድን ” ፈሪና ጀግና” በሚል እተፈራረጁ መሆኑንን በአሜሪካ የድርጅቱ ዋና ደጋፊ መናገራቸው ተሰማ። በረሃ የወረዱት ” ጅግና” ሲባሉ፤ ከተማ ተደብቀው የነበሩ ” ፈሪ” እየተባሉ ነው።
ትህነግ ከበረሃ ወጥቶ ወደ መቀለ ሲገባ ከተደበቁበት ከወጡት መካከል ዳንዔል ብርሃኔ ይገኝበታል። የድርጅቱ ዋና ደጋፊ እንዳሉት እነ ዳንኤል የሳተላይት ስልክ እንዳይጠቀሙ ተከልክለዋል። ለዚህም ምክንያቱ ” ፈሪ” በመሆናቸው ነው።
ለወትሮው ከማህበራዊ ገጽ የማይጠፋውና ወደ መቀለ ከሄደ በሁዋላ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይን በመስደብ፣ በማሽሟጠጥና በማውገዝ ስራ ተሰማርቶ የነበረው ዳንዔል፣ መንግስት እንዴት እንደሚቀየር፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዴት የዓለሙ የጦር ወንጀለኞች ፍርድ ቤት እንዴት እንደሚቀርቡ፣ ጦርነቱ ከሁለት ሳምንት በላይ እንደማይፈጅ በተደጋጋሚ በማስረዳት ቀዳሚ ነበር።
ተደብቆ ሕይወቱን ያተረፈው ዳንዔል ስልክ ፈልጎ ማጣቱን ከላይ የተገለጹት የትህነግ ዋና አባል በስሞታ ደረጃ ከሌሎች መስማታቸውን አስታውቀዋል። ቀደ ባለው ጊዜ ዳኒ የጌታቸው አሰፋ ወገን እንደነበር በተደጋጋሚ ሲነገር ነበር። “የደህንነቱ ሹም አለመኖራቸው ዳኒ ስልክና ኢንተርኔት ብርቁ ሆነ” ሲል የሰማውን ወሬ ያጋራን የአሜሪካ ተባባሪያችን ነው።
እንደ ዳኒ ሁሉ በርካታ የተደበቁ የነበሩ ” ፈሪ” ተብለው ፊት እንደተነሱ ከመቀለ መረጃ ያላቸው አስታውቀዋል።
- የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ዳግም ዝርፊያ እያፈጸሙ ነው፤ የተማሪዎች መጽሃትን “የአማራ ክልል ናቸው እየሉ ቀደዋል”በአላማጣ ከተማ በተለየ መልኩ የትግራይ ክልል ታጣቂዎች በከተማዋ ውስጥ እንደሚንቀሳቀሱ ነዋሪዎች መመስከራቸውን ቢቢሲ አስታወቀ። ይህ የተገለጸው ከአለማጣ እና አካባቢው የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር… Read more: የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ዳግም ዝርፊያ እያፈጸሙ ነው፤ የተማሪዎች መጽሃትን “የአማራ ክልል ናቸው እየሉ ቀደዋል”
- በዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ችግኝ ልትተክል ነውለዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር 6 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኝ ለመትከል ዕቅድ መያዙንna ለዚህም ተግባራዊነት ከሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊየን በላይ ችግኝ መዘጋጀቱን ተገለጸ።… Read more: በዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ ሰባት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ችግኝ ልትተክል ነው
- አፍሪካ ህብረት ” የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው” የሚለው ዜና ሃሰት መሆኑን ህብረቱ አረጋግጠአፍሪካ ህብረት የውጭ ምንዛሬ አካውንቱን ወደ ሌላ አገር እንደሚያዘዋውር ተጠቅሶ በህብረቱ ስም የወጣው ዜና ሃሰት፣ ሆን ተብሎ የተቀነባበረ መሆኑን መንግስት አስታወቀ። መረጃው… Read more: አፍሪካ ህብረት ” የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው” የሚለው ዜና ሃሰት መሆኑን ህብረቱ አረጋግጠ
- አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎችባንኩ የክፍያ ሰነድ ቀረበለት። ማጣሪያ ጥያቄ ለህብረቱ አቀረበ። ሃሰት ሆኖ ተገኘና ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን ያዘ። ጉዳዩ ወደ ህግ አመራ። አሁን ምኑ ነው አፍሪካ… Read more: አፍሪቃ ህብረት ምን አሰጋውና “ገንዘቤን ወደ ሌላ አገር ለማዛወር እያሰብኩ ነው” ሲል ተንሿከከ፤ የጾምና የፍስክ ዜናዎች
- የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል 300 ቢሊዮን ብር የንግድ ባንክ ዕዳ አለብኝ አለ፤ ዕዳውና የክፍያው ጫና እንደከበደውም አስታውቋልየኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከንግድ ባንክ 300 ቢሊዮን ብር ዕዳ እንዳለበት ተገለጸ። የዕዳ ጫናውን ለማቃለል የባንክ ወልዱም ጭምር ተፅእኖ እያሳደረ መሆኑም ተመልክቷል። የኢትዮጵያ… Read more: የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል 300 ቢሊዮን ብር የንግድ ባንክ ዕዳ አለብኝ አለ፤ ዕዳውና የክፍያው ጫና እንደከበደውም አስታውቋል